በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ከያዕቆብ የተላከ ደብዳቤ—የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት ብቻ ሳይሆን ለመታዘዝ የተሰጠ ግብዣ


ያዕቆብ 1–3

ከያዕቆብ የተላከ ደብዳቤ

የእግዚአብሔርን ቃል ለመስማት ብቻ ሳይሆን ለመታዘዝ የተሰጠ ግብዣ

ያዕቆብ ደብዳቤ እየጻፈ።

ያዕቆብ የማርያም ልጅ እና ከኢየሱስ ክርስቶስ ወንድሞች መካከል አንዱ ነበር። ያዕቆብ በኢየሩሳሌም የቤተክርስቲያን መሪ ነበር። በአለም ዙርያ ለነበሩ የእግዚአብሔር ህዝብ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል እንዲኖሩ ለመርዳት ደብዳቤ ጽፏል።

ያዕቆብ 1፥1

ጆሴፍ ስሚዝ መጽሐፍ ቅዱስን እያነበበ።

“ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው … እግዚአብሔርን ይለምን፣” በማለት ያዕቆብ ጽፏል። ከብዙ አመታት በኋላ፣ ጆሴፍ ስሚዝ የተባለ ወጣት እነዚህን ቃላት አነበበና ስለጥያቄዎቹ ለመጸለይ ወሰነ። በኋላም ጆሴፍ ስሚዝ፣ “የያዕቆብ ምስክርነት ዕውነት ሆኖ አገኘሁት” በማለት ተናገረ። እግዚአብሔር የጆሴፍ ስሚዝን ጸሎት መልሷል፣ የእኛንም እንደዚያው ይመልሳል።

ያዕቆብ 1፥5የጆሴፍ ስሚዝ—ታሪክ 1፥11–17፣ 26

ያዕቆብ የተሰበሰቡ ሰዎችን እያስተማረ።

ያዕቆብ ሌሎች ሰዎች የሚናገሩትን በጥንቃቄ መስማት እንዳለብን እና መቆጣት እንደማይገባም ጽፏል። ቁጡ ከሆንን እግዚአብሔርን ልናገለግለው አንችልም።

ያዕቆብ 1፥19–20

አንድ ወጣት ወንድ እና ሴት የሚያለቅስ ልጅ የያዘችን ሴት እያናገሩ።

የእግዚአብሔርን ቃል መስማት ብቻ በቂ እንዳልሆነና ልንኖረው እንደሚገባም ያዕቆብ ተናግሯል። “ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ … የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ” በማለት ጽፏል።

ያዕቆብ 1፥22

ወንዱ እና ሴቷ ልጅ አንዲት ሴት እና ህጻን ልጇ ከቤተሰቦቻቸው ጋር በሞቃት ድንኳን ውስጥ እንዲገቡ ጋበዟቸው።

ያዕቆብ የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታይ መሆን ማለት እንዲሁ እግዚአብሔርን ከማመን በላይ እንደሆነ ገልጿል። እግዚአብሔር ህያው እንደሆነ ዲያብሎስ እንኳን ያውቃል። የበረዳቸው ወይም የራባቸውን ሰዎች ስናይ፣ አልባሳትን እና ምግብን ልንሰጣቸው ይገባል። መበለቶችን እና ወላጅ አልባ ልጆችን ልንጎበኛቸው ይገባል። ያዕቆብ “ከስራ የተለየ እምነት የሞተ ነው” በማለት ጽፏል።

ያዕቆብ 1፥272፥14–20

አንድ ሰው አንድን ፈረስ ከአደጋ ለመጠበቅ እየመራው።

ያዕቆብ ቅዱሳን ሰዎችን በደግነት ማናገር እንዳለባቸውም ጭምር ማስተማር ፈልጎ ነበር። ለቃላቶቻችን መጠንቀቅ ልክ ፈረስን እንደመምራት እንደሆነ ተናግሯል። በፈረስ አፍ ውስጥ ባለ አነስተኛ የብረት ቁራጭ ትልቅን ፈረስ በልጓም ልንመራ እንችላለን። ቃላቶቻችን ትንሽ ቢሆኑም ሃይለኛ ሊሆኑ ይችላሉ።

ያዕቆብ 3፥2–3

በማዕበል ውስጥ ያለ መርከብ በትንሽ መቅዘፊያ ይመራል።

ያዕቆብ ለቃላቶቻችን መጠንቀቅ ልክ መርከብን እንደመምራት እንደሆነ ተናግሯል። መርከብ ትልቅ ቢሆን፣ ነፋስም ሃያል ቢሆን ትንሹን መቅዘፊያ ወይም መልህቅ በመቆጣጠር መርከቡን መምራት እንችላለን። የመርከቡ መሪ እንደ ቃላቶቻችን ነው። የምንለውን መቆጣጠር ከቻልን፣ ትልቅ ልዩነት ልናመጣ እንችላለን።

ያዕቆብ 3፥4–5

ሰዎች የተወሰኑ ፍራፍሬዎችን ከገለበጠው የሮሜ ወታደር ጋር እየተከራከሩ።

ያዕቆብ እንደገለጸው ክፉ ቃላት ታላቅን እሳት እንደሚያስነሳ ነበልባል ናቸው። በፍጥነት በመሰራጨት ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርሱ ይችላሉ። ለቃላቶቻችን መጠንቀቅ አስፈላጊ የሆነው በዚህ ምክንያት ነው።

ያዕቆብ 3፥5–6

ልጆች ለወታደሩ ፍራፍሬን እየሰጡ።

ወደ ሰማዩ አባታችን ለመጸለይ አንደበታችንን እንደምንጠቀም ያዕቆብ ጽፏል። ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ የሰማይ አባት ልጆች ለሆኑት ለመናገር በአንደበታችን አስጸያፊ ቃላትንም እንጠቀማለን። ያዕቆብ ይህ መሆን እንደሌለበት ይናገራል።

ያዕቆብ 3፥9–10

አንድ ሰላማዊ የውሃ ምንጭ በሚታይበት ቦታ ላይ ያዕቆብ ሰዎችን የወንጌል ትምህርት እያስተማረ።

ቅዱሳን መልካም ቃላትን እንዲናገሩ ለማስተማር፣ አንድ የውሃ ምንጭ መራራ እና ጣፋጭ ውሃን ሊያወጣ እንደማይችል አስተማረ። የበለስ ዛፍ ወይራን፣ የወይን ተክል ደግሞ በለስን ሊያፈራ አይችልም። በተመሳሳይ መልኩ፣ በልባችን መልካምነት እና ፍቅር ካለ፣ ቃላቶቻችንም እንዲሁ መልካም እና አፍቃሪ ሊሆኑ ይገባል!

ያዕቆብ 3፥11–18