በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
የብርሃን ልጆች—የኢየሱስ ክርስቶስን ምጻት እየጠበቅን በእርሱ መታመን


1 እና 2 ተሰሎንቄ

የብርሃን ልጆች

የኢየሱስ ክርስቶስን ምጻት እየጠበቅን በእርሱ መታመን

ጳውሎስ በተሰሎንቄ ቤተክርስቲያን ለነበሩ ሰዎች ደብዳቤ እየጻፈ።

በጳውሎስ ጊዜ የነበሩ ቅዱሳን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ወደ ምድር የሚመጣበትን ጊዜ በማሰብ ይደሰቱ ነበር። ተሰሎንቄ በተባለ ስፍራ ውስጥ ህይወት ለቅዱሳን እየከበደ ነበር። ይህ መሆኑ ኢየሱስ በቅርቡ እንደሚመጣ የሚያሳይ መሆን አለመሆኑ ያሳስባቸው ነበር። ጳውሎስ እነርሱን ለመርዳት ደብዳቤ ጻፈላቸው።

1 ተሰሎንቄ 4፥16–185፥1–22 ተሰሎንቄ 1፥4

ቤተሰብ ተኝተው።

ኢየሱስ ዳግም የሚመጣበትን ቀንና ሰዓት ማንም እንደማያውቅ ጳውሎስ ተናገረ። ልክ በተኙበት ጊዜ በሌሊት ሌባ በሚመጣበት አይነት፣ ይህም ለአንዳንድ ሰዎች አስገራሚ ይሆናል።

1 ተሰሎንቄ 5፥2–32 ተሰሎንቄ 2፥2

አንድ ደስተኛ ቤተሰብ በደማቅ የኩራዝ መብራት በሚያበራበት ውስጥ በአንድነት ተቀምጠው።

ነገር ግን ጳውሎስ ለቅዱሳኑ በጭለማ እንዳልሆኑ ነገራቸው። ኢየሱስ ክርስቶስን እየተከተሉ በመሆኑ ምክንያት፣ ቅዱሳን የብርሃን ልጆች ናቸው!

1 ተሰሎንቄ 5፥4–5።

አንድ ደስተኛ ቤተሰብ ወንጌልን ለሌላ ቤተሰብ ሲያካፍል።

ኢየሱስ ዳግም ከመምጣቱ በፊት ብዙ ሰዎች ከእውነት እንደሚያፈገፍጉ ጳውሎስ አብራርቶ ነበር። የብርሃን ልጆች የሆኑት ቅዱሳን ኢየሱስን እንዲከተሉ እና መምጣቱን እንዲጠባበቁ ይፈልግ ነበር። ይህን የምናደርግ ከሆነ፣ በአለም ምንም ይሁን ምን፣ ኢየሱስ ሲመለስ የተዘጋጀን እንሆናለን።

1 ተሰሎንቄ 1፥52 ተሰሎንቄ 2፥3