በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ኢየሱስ መራመድ የማይችልን ሰው ፈወሰ—አካላዊ እና መንፈሳዊ ፈውስ


ማርቆስ 2፥1–12

ኢየሱስ መራመድ የማይችልን ሰው ፈወሰ

አካላዊ እና መንፈሳዊ ፈውስ

ኢየሱስ በሰዎች የተሞላ ቤት ውስጥ ሲያስተምር።

ብዙ ሰዎች ኢየሱስ ሲያስተምር ለመስማት ፈለጉ። አንድ ቀን በሰዎች በተሞላ ቤት ውስጥ ያስተምር ነበር።

ማርቆስ 2፥1–2

ሰዎች አንድን ሰው በኢየሱስ እንዲፈወስ ተሸክመው ሲያመጡ።

አራት ሰዎች መራመድ የማይችልን አንድ ጓደኛቸውን ይዘው ወደ ቤቱ መጡ። እርሱን በአልጋ ላይ መሸከም ነበረባቸው። ጓደኛቸውን ወደ ኢየሱስ ሊያመጡ ፈለጉ፣ ነገር ግን ቤቱ በሰው ተሞልቶ ስለነበር ሊገቡ አልቻሉም።

ማርቆስ 2፥3–4

ሰዎቹም ሰውየውን ወደ ቤቱ ውስጥ ሲያወርዱ።

በመሆኑም ጓደኛቸውን ወደ ቤቱ ጣሪያ አወጡት። የጣሪያውን ከፊሉን ከፍተው ጓደኛቸውን ከነአልጋው ወደ ቤቱ ውስጥ፣ በህዝቡም መካከል፣ በኢየሱስ ፊት አወረዱት።

ማርቆስ 2፥4

ኢየሱስ ሰውየውን ይቅር አለው።

ኢየሱስም እምነታቸውንበማየት፣ መራመድ የማይችለውን ሰው፣ “ልጄ ሆይ፣ ሃጢያትህ ተሰረየችልህ” አለው።

ማርቆስ 2፥5

አንዳንድ የአይሁድ መሪዎች ተበሳጩ።

አንዳንድ የአይሁድ መሪዎች፣ ይህንን በሰሙ ጊዜ ተበሳጩ። ኃጢአትን ይቅር ማለት የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ እንደሆነ አሰቡ።

ማርቆስ 2፥6–7

ሰውየው ተፈወሰ እናም ተነስቶ ቆመ።

ነገር ግን ኢየሱስ እነርሱ ምን እንደሚያስቡ ያውቅ ነበር። እርሱ ሃጢያትን ይቅር ለማለት ሃይል እንዳለው እንዲረዱ ለመርዳት ተዓምራትን ሰራ። ሰውየውንም፣ “ተነሳ፣ አልጋህን ተሸከምና ወደ ቤትህ ሂድ” አለው። ሰውየውም ተነስቶ ቆመ እና ተራመደ! ሁሉም ተገረሙ እና ለእግዚአብሔርም ምስጋናን አቀረቡ።

ማርቆስ 2፥8–12