በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ኢየሱስ ለምጽ የነበረባቸውን አስር ሰዎች ፈወሰ—የምስጋና አስፈላጊነት


ሉቃስ 17፥11–19

ኢየሱስ ለምጽ የነበረባቸውን አስር ሰዎች ፈወሰ

የምስጋና አስፈላጊነት

ኢየሱስ የታመሙ ሰዎችን ስብስብ ተመለከተ።

ኢየሱስ እየተጓዘ እያለ በአንዲት መንደር ገባ እናም በቆዳቸው ላይ ለምጽ የተባለ በሽታ የነበረባቸውን አስር ሰዎች አየ። ሌሎች ሰዎችን በሽተኛ እንዳያደርጉ ለምጽ የነበረባቸው ሰዎች ከሌላው ህብረተሰብ፣ ከቤተሰባቸውም እንኳ፣ ራቅ ማለት ነበረባቸው።

ሉቃስ 17፧11-12

ሰዎቹም ኢየሱስን እንዲፈውሳቸው ጠየቁት።

ሰዎቹ ወደ ኢየሱስ በመጣራት እንዲፈውሳቸው ጠየቁት። ኢየሱስም በከተማ ወዳሉ ካህናት እንዲሄዱ ነገራቸው። ካህናት ብቻ ነበሩ ዳግም ከህዝቡ ጋር እንዲሆኑ ሊወስኑ የሚችሉት።

ሉቃስ 17፥13-14፤ በተጨማሪ ዘሌዋውያን 14፥2-3ተመልከቱ።

ሰዎቹም ተፈወሱ።

አስሩ ሰዎች ወደ ካህናት እየተጓዙ እያለ ተዓምሩ ተከናወነ። ህመማቸው ተወገደ። ተፈወሱ!

ሉቃስ 17፥14

ከመካከላቸው አንዱ ስለተፈወሰ እግዚአብሄርን አመሰገነ።

ከሰዎቹ አንዱ እንደተፈወሰ ባየ ጊዜ፣ ተመልሶ መጣ፣ በታላቅም ድምጽ እግዚአብሔርን አመሰገነ። እርሱ ሳምራዊ ነበር።

ሉቃስ 17፥15-16

ኢየሱስ ከዚህ ሰው ጋር ስለ እምነት ሲነጋገር።

እርሱም ኢየሱስ ስላደረገው ነገር በእግሩ ስር ወደቀ። ኢየሱስም የተፈወሱት ሌሎች ዘጠኙ ሰዎች ወዴት እንዳሉ ጠየቀ። አንድ ሰው ብቻ ሊያመሰግነው ተመልሶ መጣ! ኢየሱስም “ተነሣና ሂድ፤ እምነትህ አድኖሃል” አለው።

ሉቃስ 17፥16-19