የሐዋርያት ስራ 8፥5–24
ስምዖን እና የእግዚአብሔር ኃይል
ስለ እግዚአብሔር ክህነት መማር
ስምዖን የሚባል አንድ ሰው በሰማርያ ይኖር ነበር። የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል በሰማ ጊዜ አመነ። በተጨማሪም የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት በእግዚአብሔር ኃይል ባደረጉት ተአምራት ተገረመ። ስምዖን ተጠመቀ፤ በሰማርያ የነበሩ ሌሎች ብዙ ወንዶችና ሴቶችም ተጠመቁ።
የሐዋርያት ስራ 8፥5–13
በኢየሩሳሌም የነበሩት ሐዋርያት በሰማርያ የሚኖሩ ሰዎች እየተጠመቁ መሆኑን ሰሙ። ጴጥሮስና ዮሐንስ ወደ ሰማርያ ሄዱ። የእግዚአብሔርን ኃይል ተጠቅመው በተጠመቁት ሰዎች ላይ እጃቸውን ጭነው የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ ሰጧቸው።
የሐዋርያት ስራ 8፥14–17
ስምዖን ጴጥሮስንና ዮሐንስን ይህን ሲያደርጉ ባየ ጊዜ ገንዘብን አቀረበላቸውና፣ “ለእኔ ደግሞ ይህን ሥልጣን ስጡኝ” አላቸው። የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ መስጠት እንዲችል የእግዚአብሔርን ክህነት መግዛት ፈለገ።
የሐዋርያት ስራ 8፥18–19
ጴጥሮስ ማንም ሰው የእግዚአብሔርን ኃይል ሊገዛ እንደማይችል ገለጸለት። ከእርሱ የተሰጠ ስጦታ ነው። ጴጥሮስ ልቡ መለወጥ እንዳለበት ለስምዖን ነገረው። ስምዖንን ንስሐ እንዲገባና ይቅርታ እንዲጠይቅ ወደ እግዚአብሔር እንዲጸልይ ጋበዘው።
የሐዋርያት ስራ 8፥20–23
ስምዖን አዘነ። እርሱ እንዲለወጥ እንዲረዳው ጴጥሮስ እንዲጸልይለት ጠየቀው።
ከሐዋርያት ስራ 8፥24