ማቴዎስ 21፥1-16
ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ተጓዘ
ህዝቡም አዳኛቸውን ተቀበሉ
ለአይሁድ አስፈላጊ የሆነው የፋሲካ በዓል ሊከበር የተቃረበበት ጊዜ ነበር። አያሌ ሰዎችም ለፋሲካ በዓል ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘዋል። ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱም እንዲሁ ሄደዋል። ኢየሱስ መምጣቱን ህዝቡ በሰሙ ጊዜ፣ ሊያገኙት ሄዱ።
ማቴዎስ 21፥1፤ ዮሐንስ 12፥12-13
ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ ወደ ኢየሩሳሌም በቀረቡ ጊዜ፣ አህያ ያመጡለት ዘንድ ጠየቃቸው። ከብዙ ዓመታት በፊት፣ አንድ ነቢይ አዳኝ የሆነ እርሱ በአህያ ውርንጫ ትሁት ሆኖ እንደሚመጣ ተናግሯል።
ማቴዎስ 21፥1-7፤ በተጨማሪ ዘካርያስ 9፥9ተመልከቱ።
ኢየሱስ ወደ ከተማው በአህያ ጀርባ ሆኖ ገባ። ህዝቡም ስላዩት እጅግ ተደሰቱ። እንደንጉስም ተቀበሉት። አህያይቱም ትራመድበት ዘንድ የዘንባባ ዝንጣፊ እና ልብሳቸውን በመሬት ላይ አነጠፉ። እግዚአብሔርንም እያመሰገኑ፣ “ሆሣዕና፦ በእግዚአብሔር ስም የሚመጣ የእስራኤል ንጉሥ የተባረከ ነው’’ በማለት ጮኹ።
ማቴዎስ 21፥8-9፤ ሉቃስ 19፥36-38፤ ዮሐንስ 12፥13
አያሌ ህዝብም በኢየሩሳሌም የሆነው ነገር ግራ አጋብቷቸው ነበር። ‘’ይህ ማነው?’’ በማለት ጠየቁ። ሌሎችም የናዝሬቱ ኢየሱስ ነው በማለት መለሱ።
ማቴዎስ 21፥10-11
በመቀጠልም ኢየሱስ ወደ ቤተ መቅደስ ሄደ። አንዳንድ ስዎች ገንዘብ ይለዋወጡ ነበር እና ለመስዋእት የሚሆን እንሰሳም ይገዙ ነበር። ኢየሱስ ታማኝ እንዳልሆኑ አውቋል።
ማቴዎስ 21፥12
ኢየሱስ በቤተ መቅደስ ለአምልኮ ከመጡ ሰዎች ላይ ገንዘብ መቀበላቸውን አልወደደውም። እንዲሄዱ አደረጋቸው እናም ጠረቤዛዎቻቸውን ገለባበጠባቸው። እርሱም፣ ‘’ቤቴ የጸሎት ቤት ይባላል፤ ነገር ግን እናንተ የወንበዴዎች ዋሻ አደረጋችሁት’’ አላቸው።
ማቴዎስ 21፥12-13፤ በተጨማሪ ኢሳያስ 56፥7፤ ኤርሚያስ 7፥11ን ይመልከቱ።
አይነ ስውር የነበሩ ወይም መራመድ የተሳናቸው ሰዎች ጌታ ወዳለበት ወደ ቤተ መቅደስ መጡ፣ እናም ፈወሳቸው። ልጆችም ‘’ሆሳዕና፣’’ እርሱ አዳኝ ነው በማለት እያወደሱት ጮኹ።
ማቴዎስ 21፥14-15
አንዳንድ ካህናት እና ጸሃፍት ኢየሱስ ያደረገውን ነገር እና ልጆችም ሲናገሩ የነበረውን ነገር በሰሙ ጊዜ ተበሳጩ። እግዚአብሄር ከህጻናት አንደበት ፍጹም የሆነ ምስጋናን እንደሚያወጣ በቅዱስ መጽሀፍ የተነገረውን አስታወሳቸው።
ማቴዎስ 21፥15-16፤ በተጨማሪ መዝሙር 8፥2ተመልከቱ።