የሐዋርያት ስራ 16፥9–40
ጳውሎስና ሲላስ
ከጌታ በመጣ ተአምራት ዳኑ
ጌታ ጳውሎስና ሲላስ ወንጌልን በአንድነት እንዲሰብኩ ጠራቸው። በዚያ ያሉ አብያተ ክርስቲያናት እንዴት እንደሚሠሩ ለማየት ወደ ብዙ ከተሞች ተጓዙ።
የሐዋሪያት ሥራ 15፥40–41፤ 16፥4–8
አንድ ሌሊት ጳውሎስ በራእይ ከመቄዶንያ የመጣ አንድ ሰው ወደ ከተማው እንዲመጣ ሲለምነው አየ። ጳውሎስና ሲላስ ወዲያው ሄዱ። እግዚአብሔር እንዲሄዱ እንደሚፈልግ ያውቁ ነበር።
የሐዋርያት ስራ 16፥9–10
ወደ መቄዶንያ በደረሱ ጊዜ ልድያ የተባለች አንዲት ሴት ሲያስተምሩ ሰማች። ጌታ የልዲያን ልብ ከፈተ። ጳውሎስ ያስተማረውን አምና ተጠመቀች።
የሐዋርያት ስራ 16፥13–15
ልድያ ለጳውሎስና ለሲላስ በዚያ እያሉ በቤቷ ውስጥ መቆየት እንደሚችሉ ነገረቻቸው።
ከሐዋርያት ስራ 16፥15
ነገር ግን ጳውሎስና ሲላስ እዚያ መኖራቸውን ሁሉም አልወደዱም። አንዳንዶቹ የሚያስተምሩትን አልወደዱም። ጳውሎስንና ሲላስን ወደ ገበያ ወሰዱ እናም ለከተማይቱ አለቆች እነርሱ ሁከት እየፈጠሩ እንደሆነ ነገሯቸው።
የሐዋርያት ስራ 16፥16–21
ሕዝቡም በጳውሎስና በሲላስ ላይ ተቈጡ። የከተማይቱም አለቆች የጳውሎስንና የሲላስን ልብስ ቀደዱ እንዲሁም ሊደበድቡ ይገባል አሉ።
የሐዋርያት ስራ 16፥22–23
ከዚያም የከተማይቱም አለቆች ጳውሎስንና ሲላስን ወደ ወኅኒ ጣሏቸው። እግራቸውንም አስረው ዘበኛ አስቀመጡባቸው።
የሐዋርያት ስራ 16፥23–24
በዚያች ሌሊት ጳውሎስና ሲላስ ሌሎቹ እስረኞች እያዳምጧቸው ሳለ ለእግዚአብሔር ጸለዩ እንዲሁም መዝሙሮችን ዘመሩ። በድንገት መሬቱ መንቀጥቀጥ ጀመረ። የእስር ቤቱ በሮች ተከፈቱ፣ እስራታቸውም ተፈቱ።
የሐዋርያት ስራ 16፥25–26
ዘበኛው ከእንቅልፉ ነቅቶ የተከፈቱትን በሮች ተመለከተ። እስረኞቹ እንዳመለጡ እና እንዲያመልጡ በመፍቀድ ችግር ውስጥ እንደሚገባ አስቦ ነበር። ጳውሎስ ዘበኛው እንዳይጨነቅ ነገረው። እስረኞቹ ሁሉ እዚያው ነበሩ።
የሐዋርያት ስራ 16፥27–28
ዘበኛው ፈርቶ ነበር። ጳውሎስና ሲላስ አጠገብ ተንበረከከ እናም እንዲህ አለ፣ “ለመዳን ምን ማድረግ ይገባኛል?” እነርሱም፣ “በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ እመን” አሉት።
የሐዋርያት ስራ 16፥27–31
ጳውሎስና ሲላስ ወንጌልን ለዘበኛውን እና ለቤተሰቡ አስተማሩ። ዘበኛው የጳውሎስንና የሲላስን ቁስል አከመ። በዚያች ምሽት እሱና ቤተሰቡ ተጠመቁ።
የሐዋርያት ስራ 16፥32–33