የሐዋሪያት ሥራ 6–7
እስጢፋኖስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መሰከረ
ደፋር አገልጋይ ለምስክርነቱ ሕይወቱን አሳልፎ ሰጠ
ቤተክርስቲያኗ በፍጥነት እያደገች ነበር። ሁሉንም አባላት ለመንከባከብ ለሐዋርያቱ አስቸጋሪ እየሆነ መጣ።
የሐዋርያት ስራ 6፥1–2
ሐዋርያትም ሊረዱ የሚችሉ ሰባት ሰዎችን ለመጥራት ወሰኑ። እነርሱም ጥበበኞችና መንፈስ ቅዱስ የተሞሉ ሰዎችን እንዲፈልጉ አባላትን ጠየቁ።
የሐዋሪያት ስራ 6፥3
ከተመረጡት ሰዎች አንዱ እስጢፋኖስ ነበር። ሐዋርያትም ቡራኬን ሰጡት። እስጢፋኖስ ብዙ እምነት ነበረው እናም በሕዝቡ መካከል ታላላቅ ተአምራትን አደረገ።
የሐዋርያት ስራ 6፥5–8
እስጢፋኖስ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ በጥበብና በመንፈስ አስተማረ። የምኩራብ አለቆች ግን ያስተምረውን ነገር አልወደዱትም። ሙሴንና እግዚአብሔርን ተሳድቧል አሉት። እስጢፋኖስን በሊቀ ካህናቱና በሌሎች መሪዎች ፊት አመጡት።
የሐዋሪያት ሥራ 6፥9–15፤ 7፥1
የእስጢፋኖስ ፊት የመልአክ ፊት ይመስል ነበር። እስራኤልን ለማዳን እግዚአብሔር ሙሴን እንደላከ፣ ነገር ግን ሕዝቡ ሙሴን ሁልጊዜ እንደዳልተከተለው ለመሪዎቹ አስተውሳቸው። እስጢፋኖስ ሙሴ እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ተናገረ። እግዚአብሔር ሕዝቡን እንዲያድን ኢየሱስን ላከ፣ ቢሆንም መሪዎቹ ግን አልተከተሉትም። መሪዎቹም በእስጢፋኖስ ላይ ተናደዱ።
የሐዋርያት ስራ 7፥20–43፣ 51–54
እስጢፋኖስ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልቶ ወደ ሰማይ ተመለከተ። ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማይ አባት አጠገብ ቆሞ አየ።
የሐዋርያት ስራ 7፥55–56
እስጢፋኖስ ያየውን ለመሪዎቹ ሲነግራቸው የበለጠ ተበሳጩ። እነርሱም በቁጣ ጮኹ እና እስጢፋኖስን ያዙት። ከዚያም እርሱን ከከተማይቱ ጎትተው አውጥተው ወሰዱት።
ከሐዋርያት ስራ 7፥57
ሳኦል በሚሉት በአንድ ሰው እግር አጠገብ ልብሳቸውን ጣሉ። እስጢፋኖስን ሊገድሉት ድንጋይ ወረወሩበት። ሳኦልም በሚያደርጉት ነገር ተስማማ። እስጢፋኖስ ጸለየ። የጎዱትን ሰዎች ይቅር እንዲላቸውም ጌታን ጠየቀ። በተጨማሪም ጌታ መንፈሱን ወደ ሰማይ እንዲቀበለው ጠየቀ።
የሐዋሪያት ሥራ 7፥59–60፤ 8፥1