ማርቆስ 10፥17–31
ኢየሱስና ሀብታሙ ወጣት
“የዘላለም ሕይወትን እወርስ ዘንድ ምን ላድርግ?”
ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ በመንገድ ላይ እያሉ፣ አንድ ሀብታም ወጣት ሰው ወደ ኢየሱስ ሮጦ በፊቱ ተንበረከከ። ከሰማይ አባት ጋር እንደገና ለመኖር ምን ማድረግ እንደሚገባው ኢየሱስን ጠየቀ።
ማርቆስ 10፥17
ኢየሱስ ወጣቱ ሰው ስለ እግዚአብሔር ትእዛዛት እንደሚያውቅ አስታወሰው፦ አትግደል፣ አትዋሽ ወይም አትስረቅ፣ እንዲሁም አባት እና እናትህን አክብር።
ማርቆስ 10፥19
ወጣቱም ሰው እነዚህን ትእዛዛት ከልጅነቱ ጀምሮ ያከብራቸው እንደነበር መልስ ሰጠ።
ማርቆስ 10፥20
ኢየሱስ ወጣቱን ሰው በፍቅር ተመለከተው። አንድ ተጨማሪ ነገር ማድረግ እንዳለበት ነገረው። ያለውን ነገሮች በሙሉ መሸጥ፣ ገንዘቡን ለድሆች መስጠት፣ እና ከኢየሱስ ተከታዮች አንዱ መሆን ያስፈልገው ነበር። ከዚያም የሰማይ ሀብቶች ይኖሩታል።
ማርቆስ 10፥21
ወጣቱ በጣም ሀብታ ነበር። ያልወን ነገሮች ሁሉ ለመስጠት አልፈለገም። አዝኖም ሄደ።
ማርቆስ 10፥22
ኢየሱስም ሀብትን የሚወዱ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ከመግባት ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል አለ። ደቀመዛሙርቱ ተገርምመው ነበር። “እንግዲያ ማን ሊድን ይችላል?” ብለው ጠየቁ። ኢየሱስ ለመዳን እግዚአብሔርን ማመን እንዳለብን ገለጸ። እርሱም “በእግዚአብሔር ዘንድ ሁሉ ይቻላልና” አለ።
ማርቆስ 10፥23–30