በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
በኢየሱስ ክርስቶስ እምነት መኖር—እርሱ “የእምነታችን ጀማሪ እና ፈጻሚ ነው”


ዕብራውያን 11–12

በኢየሱስ ክርስቶስ እምነት መኖር

እርሱ “የእምነታችን ጀማሪ እና ፈጻሚ” ነው

አንድ ሰው እና አንዲት ወጣት ሴት ሰዎች ንብረታቸውን ሲያወድሙባቸው እየተመለከቱ።

በቀድሞዋ ቤተክርስቲያን ውስጥ የኢየሱስ ክርስቶስ ተከታይ መሆን ሁልጊዜ ቀላል አልነበረም። አንዳንድ ጊዜ በእምነታቸው ምክንያት ሰዎች የቤተክርስቲያን አባላትን ይጠሏቸው ወይም ይሳለቁባቸው ነበር። ጳውሎስ በኢየሱስ ክርስቶስ ያለውን እምነታቸውን እንዲጠብቁ ሊረዳቸው ይፈልግ ነበር።

ዕብራውያን 10፥32–39

ጳውሎስ በፊት እየታየ፣ አንድ ሰው እና አንዲት ወጣት ሴት ሲጸልዩ።

ጳውሎስ ለዕብራውያን፣ ወይም ለአይሁድ፣ ቅዱሳን ደብዳቤ ጻፈላቸው። እምነት ማለት ምንም እንኳ ልናየው ባንችልም በአንድ ነገር ማመን ወይም ተሳፋ ማድረግ እንደሆነ አስተማረ። ለምሳሌ፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን ማለት ተስፋ ያደረግናቸውን በረከቶች ባንቀበልም እንኳ እርሱን እና የተስፋ ቃሉን ማመን ማለት ነው።

ዕብራውያን 11፥1፣ 6

አንድ ሰውዬ እምነት ስለነበራቸው ሰዎች ታሪክ ሲያነብ አንዲት ሴት ፈገግ እያለች።

የዕብራውያን ቅዱሳን ፈተናዎቻቸውን በእምነት እንዲወጡ ለመርዳት፣ ጳውሎስ በቅዱሳት መጻህፍት ውስጥ ታላቅ እምነት ስለነበራቸው ሰዎች አስታወሳቸው።

ዕብራውያን 11፥4–40

ኖኅ መርከብን ለመስራት መመሪያን እየተመለከተ።

ለምሳሌ፣ ጳውሎስ ስለኖህ ተናገረ። እግዚአብሔር ኖህ ቤተሰቡን ከጎርፍ ለማዳን መርከብ መስራት እንዳለበት ነግሮት ነበር። ኖህ ዝናብን ከማየቱ በፊት እንኳ ለመታዘዝ እምነት ነበረው።

ዕብራውያን 11፥7

አብርሐም እና ሣራ ቤታቸውን ትተው እየሄዱ።

እግዚአብሔር ወደ ተሻለ ስፍራ እንደሚመራቸው ቃል ስለገባላቸው ስለአብርሃም እና ሳራ ጳውሎስ ተናገረ። ምንም ያረጁ ቢሆን እና ልጆች ባይኖሯቸውም፣ ታላቅ ቤተሰብ እንደሚኖራቸው እግዚአብሔር የሰጣቸውን የተስፋ ቃል እንዲሁ አምነዋል።

ዕብራውያን 11፥8–16

የሙሴ እናት እና እህት በቅርጫት ውስጥ እርሱን እየደበቁ።

ጳውሎስ ስለሙሴ እናት፣ ስለ አያቤድ እንዲሁ ተናግሯል። እርሱ ህጻን እያለ ክፉ ከሆነው ንጉስ ልትጠብቀው ለመደበቅ እምነት ነበራት።

ዕብራውያን 11፥23

ሙሴ አንድ ግብጻዊ እስራኤላዊን ሲተናኮለው እየተመለከተ።

ሙሴ ግብጽ ውስጥ አደገ። ባለጠጋ እና የተመቸው መሆን ይችል ነበር። ነገር ግን በእግዚአብሔር እና በበረከቱ ላይ እምነት ስለነበረው ያንን ሁሉ ተወ።

ዕብራውያን 11፥24–27

ሙሴ ቀይ ባህርን እየከፈለ።

በእምነቱ ምክንያት ሙሴ የእግዚአብሔርን ህዝብ ከባርነት ሊያወጣ ችሏል። እነርሱ በቀይ ባሕር በኩል በደረቅ መሬት ተራምደው ተሻግረዋል።

ዕብራውያን 11፥29

ረዓብ ከልጆቿ ጋር።

ጳውሎስ ስለረዓብም እንዲሁ ተናግሯል። በከተማዋ ውስጥ ሌላ ማንም ጌታን ባላመነበት ጊዜ፣ የእግዚአብሔርን ህዝብ ለመርዳት እምነት ነበራት። እምነቷ ቤተሰቧን አድኗል።

ዕብራውያን 11፥30–31

አንድ ሰውዬ እና አንዲት ልጅ የጠገኑትን ማሰሮ እየተመለከቱ።

ህይወት ከባድ ቢሆንም፣ እነዚህ አያሌ የእምነት ምሳሌዎች በኢየሱስ ክርስቶስ እንድናምን ሊረዱን እንደሚችሉ ጳውሎስ ተናግሯል። ንሰሃ ልንገባ እና “የእምነታችን ጀማሪ እና ፈጻሚ” የሆነውን ኢየሱስን መመልከት እንችላለን። የሃጢያት ክፍያው ታላቅ ደስታ እና ፈውስ እንደሚያመጣልን ስላወቀ ለእኛ ለመሞት ፈቃደኛ ነበር!

ዕብራውያን 12፥1–2