ማቴዎስ 25፥14–30
የመክሊት ምሳሌ
የመክሊት ምሳሌ—እግዚአብሔር የሰጠንን ነገር በአግባቡ መጠቀም
ስለእግዚአብሔር መንግስት ለማስተማር፣ ኢየሱስ ምሳሌን ተናገረ። በምሳሌው ውስጥ፣ አንድ ሰው ወደ ሩቅ አገር ለመጓዝ እየተዘጋጀ ነበር። ከመሄዱ በፊት፣ ከአገልጋዮቹ መካከል ከሶስቱ ጋር ተገናኘና በጎዞ ላይ ሳለ ገንዘቡን እንዲጠብቁለት ጠየቃቸው።
ማቴዎስ 25፥14
ሰውየው ለእያንዳንዱ አገልጋዮቹ መክሊት ተብሎ የሚጠራ ብዙ ገንዘብ ሰጣቸው። ለአንዱ አገልጋይ አምስት መክሊት ሰጠ። ለሌላው አገልጋይ ሁለት መክሊት ሰጠ። እንዲሁም ለመጨረሻው አገልጋይ አንድ መክሊት ሰጠ። ከዚያም ወደጉዞው ሄደ።
ማቴዎስ 25፥15
አምስት መክሊት የተቀበለው አገልጋይ ጠንክሮ ሰራ። መክሊቱን በመጠቀም ተጨማሪ አምስት ትርፍ መክሊት አገኘ።
ማቴዎስ 25፥16
አምስት መክሊት የተቀበለው አገልጋይ ጠንክሮ ሰራ። መክሊቱን በመጠቀም ተጨማሪ ሁለት ትርፍ መክሊት አገኘ።
ማቴዎስ 25፥17
አንድ መክሊት የተቀበለው አገልጋይ ምድርን ቈፈረና መክሊቱን ቀበረ።
የማቴዎስ 25፥18
ከጊዜ በኋላ ሰውየው ከጉዞው ተመለሰ። አገልጋዮቹ በሰጣቸው መክሊት ምን እንደሠሩ ለማወቅ ፈለገ።
ማቴዎስ 25፥19
አምስት መክሊት የተቀበለው አገልጋይ እና ሁለት መክሊት የተቀበለው አገልጋይ ጌታቸው በጉዞ ላይ እንዳለ እንዴት ሁለት እጥፍ ትርፍ እንዳገኙ ነገሩት። ጌታውም ተደሰተ። ታማኝ ስለነበሩ ይበልጥ በብዙ ነገር ላይ ሀላፊ እንዲሆኑ እንደሚያምናቸው ነገራቸው። ደስተኛ እንዲሆኑ ነገራቸው።
ማቴዎስ 25፥20–23
አንድ መክሊት የተቀበለው አገልጋይ ፈርቶ እንደነበረ፣ ስለዚህ መክሊቱን በምድር እንደደበቀው ለጌታው ነገረ። መክሊቱን ለጌታው መለሰ።
ማቴዎስ 25፥24–25።
ጌታው በአገልጋዩ አልተደሰተም ነበር። አገልጋዩ የተሰጠውን ተጠቅሞ ተጨማሪ መክሊቶችን ማትረፍ ነበረበት አለው። ጌታውም መክሊቱን አሥር መክሊት ላለው አገልጋይ ሰጠው። ጌታው አገልጋዮቹ የሰጣቸውን መክሊት ተጠቅመው መንግሥቱን እንዲገነቡ ፈልጎ ነበር።
ማቴዎስ 25፥26–29