በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
መላእክት ማርያምን እና ዮሴፍን ጎበኙ—የእግዜአብሔርን ልጅ ለመጠበቅ መመረጥ


ማቴዎስ 1ሉቃስ 1

መላእክት ማርያምን እና ዮሴፍን ጎብኙ

የእግዜአብሔርን ልጅ ለመጠበቅ መመረጥ

ማርያም እና ዮሴፍ ሲነጋገሩ።

ማርያም የተባለች አንዲት ሴት በናዝሬት ከተማ ውስጥ ትኖር ነበር። እግዚአብሔርን የምትወድ እና ትእዛዛቱንም የምታከብር ነበረች። ማርያምም እርሱም እንዲሁ እግዚአብሔርን ይወደ የነበረ ዮሴፍ የተባለን ሰው ልታገባ ነበር።

ማቴዎስ 1፥18–19ሉቃስ 1፥26–28

መልአኩ ገብረኤል ማርያምን ሲጎበኝ።

አንድ ቀን፣ ገብርኤል የተባለ መልአክ ማርያምን ጎበኛት። በመጀመሪያ ማርያም ፈርታ ነበር። ነገር ግን ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ የተላከ መሆኑን ተናገረ። ማርያም መፍራት አልነበረባትም። እርሱም ማርያም ለእግዚአብሔር እጅግ ልዩ እንደሆነች እና በቅርቡም ልጅ እንደምትወልድ ተናገረ። የማርያም ልጅ የእግዚአብሔር ልጅ፣ ኢየሱስ ይሆናል።

ሉቃስ 1፥26–33

መልአኩ ለማርያም ልጅ እንደምትወልድ ሲነግራት።

ነገር ግን ማርያም ግራ ታጋብታ ነበር። ከዮሴፍ ጋር ገና አልተጋባችም ነበር። እንዴት ልጅ ልትወልድ ትችላለች? ገብረኤልም ይህ በእግዚአብሔር ሃይል እንደሚከሰት አብራራ። “ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና” ብሎ ነገራት።

ሉቃስ 1፥34–37

ማርያም የእግዚአብሔር ልጅ እናት ለመሆን ፈቃደኛ እንደሆነች ለመልአኩ ስትናገር።

ማርያም ትሁት እና ታማኝ ነበረች። እርሷ ለገብረኤል የእግዚአብሔር አገልጋይ እንደሆነች ተናገረች። እርሷ የእግዚአብሔር ልጅ እናት ለመሆን ፈቃደኛ ነበረች።

ሉቃስ 1፥38

ዮሴፍ ማርያም ልጅ እንደምትወልድ ሲያውቅ።

ዮሴፍ፣ ማርያም ልጅ እንደምትወልድ ባወቀ ጊዜ ተረበሸ። አሁንም ማርያምን ማግባት እንዳለበት አሰበ።

ማቴዎስ 1፥19

መልአክ ለዮሴፍ ሲገለጥ።

ነገር ግን በአንድ ሌሊት በህልሙ አንድ መልአክ ለዮሴፍ ተገለጠ። መልአኩም የማርያም ልጅ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ እና ስሙንም ኢየሱስ ብሎ ሊሰይመው እንደሚገባ ለዮሴፍ ነገረው። ኢየሱስ ሰዎችን ሁሉ ከሃጢያታቸው ያድናቸዋል። መልአኩ አሁንም ዮሴፍ ማርያምን ማግባት እንዳለበት ተናገረ።

ማቴዎስ 1፥20–23

ማርያም እና ዮሴፍ ሲጋቡ።

ዮሴፍ መልአኩ እንደነገረው አደረገ። ማርያም እና ዮሴፍ ተጋቡ።

ማቴዎስ 1፥24።

ማርያም ዘመዷን ኤልሳቤጥን ስትጎበኝ።

ማርያም ዘመዷን ኤልሳቤጥን ለመጎብኘት ሄደች። መልአኩ ለማርያም ኤልሳቤጥ ምንም እንኳን በጣም ያረጀች ብትሆንም እርጉዝ መሆኗን ጭምር ነገራት። ይህ ከእግዚአብሔር ዘንድ ሌላው ተዓምር ነበር። ልጇም መጥምቁ ዮሐንስ ለመሆን ያድጋል። ማርያም ወደ ቤቱ ስትገባ፣ ለኤልሳቤጥ ሰላምታ ሰጠቻት።

ሉቃስ 1፧13–17፣ 36፣ 39–40

ኤልሳቤጥ እና ማርያም ሲደሰቱ።

ኤልሳቤጥ የማርያምን ድምጽ እንደሰማች፣ የኤልሳቤት ልጅ በውስጧ በደስታ ዘለለ። ኤልሳቤጥ በመንፈስ ቅዱስ ተሞላች። ማርያም የእግዚአብሔርን ልጅ እንደጸነሰች አወቀች። ማርያም ከኤልሳቤጥ ጋር ተደሰተች። እርሱ ልጆቹን ለመባረክ እያደረገ ላለው አስደናቂ ነገሮች ሁሉ እግዚአብሔርን አወደሰች።

ሉቃስ 1፥41–55