ኤፌሶን 6፥11–17
የእግዚአብሔር ሙሉ የጦር ዕቃ
በመንፈሳዊነት ተጠብቆ መቆየት
ጳውሎስ በኤፊውሶን ለነበሩት ቅዱሳን ሁላችንም ከክፉው ጋር መንፈሳዊ ውጊያ ውስጥ እንዳለን አስተማረ። ልክ ወታደሮች በውጊያ ወቅት አካላቸውን በጦር ዕቃ እንደሚሸፍኑ ሁሉ፣ እኛም መንፈሳችንን ለመጠበቅ መንፈሳዊ የጦር ዕቃችንን መልበስ እንችላለን።
ኤፌሶን 6፥11–13
የወታደርን የጦር እቃ በመንፈስ ከሚጠብቁን ነገሮች ጋር አነጻጽሮታል። ለምሳሌ፣ እውነት በወገባችን እንደምንታጠቀው ዝናር ወይም ቀበቶ ነው አለ።
ኤፌሶን 6፥14
በመቀጠልም፣ ጳውሎስ ጽድቅ ደረታችንን እንደሚሸፍን የደረት ጥሩር ነው አለ።
ኤፌሶን 6፥14
የኢየሱስ ክርስቶስ የሰላም ወንጌል እግራችንን እንደሚሸፍን መጫሚያ ነው።
ኤፌሶን 6፥15
ልክ ጋሻ ወታደሮችን ከጠላቶቻቸው ቀስት እንደሚከላከላቸው፣ በኢየሱስ ክርስቶስ ያለን እምነት ከሰይጣን የሚከላከለን ጋሻ ነው።
ኤፌሶን 6፥16
ጳውሎስ ደህንነት ራሳችንን እና አዕምሮአችንን እንደሚጠብቅ የራስ ቁር ነው አለ።
ኤፌሶን 6፥17
በመጨረሻም፣ ጳውሎስ መንፈስ እና የእግዚአብርሔር ቃል እንደሰይፍ ናቸው አለ።
ኤፌሶን 6፥17
እያንዳንዱን የእግዚአብሔር የጦር ዕቃ በለበስን ጊዜ፣ የሰይጣንን ውሸት እና ፈተና በመቋቋም በጀግንነት መቆም እንችላለን። መንፈሳችን በደህንነት እና በብርታት አንዲጠበቁ ለመርዳት እግዚአብሔር ይህን የጦር ዕቃ ሰጥቶናል።
ኤፌሶን 6፥11–13