ማርቆስ 5፥21–43
ኢየሱስ አንዲትን ሴት ፈወሰ እንዲሁም የኢያኢሮስን ሴት ልጅ ከሞት አስነሳ
“እመን ብቻ እንጂ አትፍራ”
ኢያኢሮስ የተባለ ሰው በገሊላ ባህር አጠገብ ባለች ከተማ ውስጥ ከሚስቱ እና ከሴት ልጁ ጋር ይኖር ነበር። ኢያኢሮስ አይሁድ እግዚአብሔርን በሚያመልኩበት ምኩራብ ውስጥ አለቃ ነበር።
ማርቆስ 5፥22
የ12 ዓመት እድሜ የነበራት የኢያኢሮስ ሴት ልጅ እጅግ ታምማ ነበር። ለሞትም ተቃርባ ነበር። ኢያኢሮስ እርዳታ እንደሚያስፈልጋት አውቋል። ኢየሱስ እነርሱ በሚኖሩበት ከተማ እንደነበርም አውቋል።
ማርቆስ 5፥22–23
ኢያኢሮስ ቤቱን ትቶ ሄደ እናም ኢየሱስን አገኘ። እርሱም በኢየሱስ እግር ስር ወደቀ እናም እንዲመጣ እና ልጁን እንዲፈውስለት ለመነው። ኢየሱስ ሴት ልጁን ቢባርክለት እርሷም መኖር እንደምትችል ኢያኢሮስ ያውቅ ነበር። ኢየሱስ ኢያኢሮስን ተከትሎ ወደ ቤቱ ሄደ። ብዙ ህዝብም ተከተሉት።
ማርቆስ 5፥23–24
በዚሁ ከተማ የነበረች አንዲት ሴት እንዲሁ የኢየሱስን እርዳታ ፈለገች። ለ12 ዓመታት በህመም ትሰቃይ ነበር። ያላትን ሁሉ በህክምና ባለሙያዎች ላይ አባከነች፣ ነገር ግን የሚፈውሳት አልነበረም— እየባሰባት ሄደች። እርሷም ኢየሱስ ሊፈውሳት እንደሚችል አውቃ ነበር። ነገር ግን በህዝቡ መካከል አልፋ እርሱን እንዴት ልታገኘው ትችላለች?
ማርቆስ 5፥25–27
ሴቲቱም የኢየሱስን የልብሱን ጫፍ ብቻ ብትነካ ልትፈወስ እንደምትችል አመነች። ኢየሱስ ሲያልፍ እሱን ለመንካት እጇን ዘረጋች። የልብሱን ጫፍ እንደነካች ወዲያውኑ ከህመሟ ተፈወሰች።
ማቴዎስ 9፥20፤ ማርቆስ 5፥27–29፤ ሉቃስ 8፥44
ወዲያውኑም ኢየሱስ መጓዙን አቆመ። ሀይል ከእርሱ እንደወጣ ተሰማው። “የዳሰሰኝ ማን ነው?” በማለት ጠየቀ። ደቀ መዛሙርቱም ግራ ገብቷቸው ነበር። ብዙ ሰዎች ነክተውታል—በህዝብ ተከብበው ነበር። ኢየሱስ ማን እንደነካው ለማወቅ ዘወር ብሎ አየ።
ማርቆስ 5፥30–32፤ ሉቃስ 8፥45
ኢየሱስ ልብሱን የነካችው ሴት ማን እንደሆነች አየ። ስለ ህመሟ ለኢየሱስ ነገረችው፥ ኢየሱስም እንደፈወሳት ተናገረች። ኢየሱስ እንድትጽናና ነገራት። በእርሱ ባላት እምነት ምክንያት ተፈውሳለች። እርሱም “በሰላም ሂጂ፣” አላት።
ማርቆስ 5፥33–34፤ ሉቃስ 8፥47–48
ከዚያም ከኢያኢሮስ ቤት አንድ ሰው መጣ። አሁን በጣም ዘግይቷል፤ የኢያኢሮስ ሴት ልጅ ሞታለች በማለት ተናገረ። ኢያኢሮስም ከዚህ በኋላ ኢየሱስን ሊያስጨንቀው አይገባውም።
ማርቆስ 5፥35
ወዲያውኑም ኢየሱስ ይህን እንደሰማ፣ “እመን ብቻ እንጂ አትፍራ” በማለት ለኢያኢሮስ ነገረው። ከዚያም ወደ ኢያኢሮስ ቤት ሄዱ።
ማርቆስ 5፥36–38
ኢያኢሮስ እና ሚስቱ ልጃቸው ተኝታ ወዳለችበት ኢየሱስን መሩት። ኢየሱስም የልጅቷን እጅ በመያዝ “ተነሽ እልሻለሁ” አላት።
ማርቆስ 5፥41
ወዲያውኑ፣ የኢያኢሮስ ሴት ልጅ ከአልጋዋ ላይ ተነሳች። ከእንግዲህ ወዲህ ሞታ አልነበረም! ኢየሱስ ለኢያኢሮስ እና ለሚስቱ የሚበላ ነገር እንዲሰጧት ጠየቃቸው። ኢየሱስ ለልጃቸው ያደረገው ነገር አስገርሟቸዋል። ስለዚህ ተዓምር ለሌሎች ሰዎች እንዳይናገሩ ጠየቃቸው።
ማርቆስ 5፥42–43