በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ኢየሱስ፣ አንዲት ሴት፣ እና የውሃ ጉድጓድ—ስለ ህይወት ውሃ ማስተማር


ዮሐንስ 4

ኢየሱስ፣ አንዲት ሴት፣ እና የውሃ ጉድጓድ

ስለ ህይወት ውሃ ማስተማር

ኢየሱስ ውሃን ለማግኘት በአንድ ጉድጓድ አጠገብ መቆሙ።

ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ ወደ ገሊላ ለመሄድ በሰማርያ አለፉ። ውሃን ለማግኘት በአንድ ጉድጓድ አጠገብ ቆሙ። ኢየሱስ በዚያ አረፍ ብሎ እያለ፣ ደቀመዛሙርት ምግብ ለመግዛት ሄዱ።

ዮሐንስ 4፥3–8

ኢየሱስ ክርስቶስ በጉድጓድ አጠገብ ያለችን ሴት ውሃ እንድትሰጠው ጠየቃት።

ከሰማርያ የሆነች አንዲት ሴት የውሃ ማሰሮዋን ልትሞላ ወደ ጉድጓዱ መጣች። ኢየሱስ የሚጠጣን ውሃ እንድትሰጠው ጠየቃት። ሴቲቱ ተገርማ ነበር። ኢየሱስ አይሁዳዊ ነው፣ እና አብዛኞቹ አይሁዳውያን ከሰማርያ ሰዎች ጋር አይነጋገሩም ነበር።

ዮሐንስ 4፥7–9

ኢየሱስ ሴቲቱን ስለ ወንጌል ሲያስተምር።

ኢየሱስም ከጉድጓዱ ውሃን የሚጠጡ ሰዎች ዳግም እንደሚጠሙ ነገራት። ነገር ግን እርሱ የዘለዓለም “የህይወት ውሃ” ሊሰጣት እንደሚችል እና ወደ ፊት ፈጽሞ እንደማትጠማ ነገራት። ሴቲቱም ከዚህ “የህይወት ውሃ” ጥቂት እንደምትፈልግ ነገረችው።

ዮሐንስ 4፥10–14

ኢየሱስም ሄዳ ባሏን እንድትጠራ ሲነግራት።

ኢየሱስም ሄዳ ባሏን እንድትጠራ ነገራት። እርስዋም “እኔ ባል የለኝም” አለች። ኢየሱስም አምስት ባሎች እንደነበሯት፣ እና አብሯት ይኖር የነበረው ሰው ባሏ እንዳልነበረ ነገራት።

ዮሐንስ 4፥16–18

ኢየሱስ ለሴቲቱ እርሱ አዳኝ እንደሆነ ሲነግራት።

ሴቲቱም ስለ እርሷ እነዚህን ነገሮች በማወቁ ተገረመች። እርሷም በቅርቡ አዳኝ የሆነ መምጣቱን እንደምታውቅ ተናገረች። ኢየሱስም እርሱ አዳኝ እንደሆነ ነገራት።

ዮሐንስ 4፥19፣ 25–26

ኢየሱስ በውሃው ጉድጓድ አጠገብ ብዙ ሰዎችን ሲያስተምር።

ሴቲቱም የውሃ ማሰሮዋን በጉድጓዱ አጠገብ ትታ ወደ ከተማው ሄደች። ለአያሌ ሰዎችም አዳኙን እንዳገኘችው ተናገረች። እንዲመጡ እና ሲያስተምር እንዲሰሙ ጋበዘቻቸው። በዚህች ሴት ምክንያት፣ ብዙ የሰማርያ ሰዎች በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ።

ዮሀንስ 4፥28–29፣ 39–42