በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ኢየሱስ በጌቴሴማኒ—ስለ ዓለም ኃጢአት መከራ መቀበል


ማቴዎስ 26፥36–46ሉቃስ 22፥39–46

ኢየሱስ በጌቴሴማኒ

ስለ ዓለም ኃጢአት መከራ መቀበል

ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ወደ ጌቴሴማኒ እንዲከተሉት ጠየቃቸው።

ኢየሱስና ሐዋርያቱ ጌቴሴማኒ ወደምትባል የአትክልት ስፍራ ሄዱ። ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን እንዲከተሉት ጠየቃቸው፤ ሌሎቹም እንዲጠብቁ ነገራቸው።

ማቴዎስ 26፥36–37ዮሐንስ 18፥1

ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን በሚጸልይበት ጊዜ ከእርሱ ጋር ነቅተው እንዲቆዩ ጠየቃቸው።

ኢየሱስ ለጴጥሮስ፣ ለያዕቆብና ለዮሐንስ በጣም እንዳዘነ ነገራቸው። ሲጸልይ ከእርሱ ጋር ነቅተው እንዲቆዩ ጠየቃቸው።

ማቴዎስ 26፥38

ኢየሱስ ወደ አትክልት ስፍራ ገባ።

ከዚያም ኢየሱስ ትንሽ ራቅ ብሎ ወደ አትክልቱ ሄደ። ንስሐ እንድንገባና ይቅር እንድንባል ስለ ኃጢአታችን መከራ መቀበል ጀመረ። ኢየሱስ እንዴት እንደሚረዳን እንዲያውቅ ህመማችን፣ ስቃያችን እና ሀዘናችን ሁሉ ተሰምቶት ነበር። ይህን ያደረገው ስለወደደን ነው። ይህ ሁሉ የሰማይ አባት ዕቅድ አካል ነበር።

ማቴዎስ 26፥39ሉቃስ 22፥41ሮሜ 3፥23አልማ 7፥11–133 ኔፊ 27፥19

ኢየሱስ በጌቴሴማኒ ተሠቃየ።

ኢየሱስ የደረሰበት ሥቃይ በጣም አሳዛኝ ከመሆኑ የተነሳ የሰማዩ አባት ስቃዩን ማስወገድ ይችል እንደሆነ ጠየቀው። ነገር ግን አባቱ እንዲያደርገው የሚፈልገውን ለማድረግ ፈቃደኛ ነበር። እርሱም “የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ” አለ።

ሉቃስ 22፥42

ኢየሱስ ጴጥሮስ፣ ያዕቆብና ዮሐንስ ነቅተው እንዲጸልዩ ጠየቃቸው።

ኢየሱስም ወደ ጴጥሮስ፣ ወደ ያዕቆብና ወደ ዮሐንስ ሲመለስ ተኝተው እንደነበሩ አየ። ከእንቅልፉቸው አስነሳቸው እንዲሁም ነቅተው እንዲጸልዩ በድጋሚ ጠየቃቸው። ነገር ግን ነቅተው ለመቆየት ቢፈልጉም በጣም እንደደከሙ ያውቅ ነበር።

ማቴዎስ 26፥40–41

መልአክ ኢየሱስን ሊያበረታታ መጣ።

ኢየሱስ እንደገና ጸለየ። አንድ መልአክ ማበረታቻ ሊሰጠው መጣ። በጣም ስቃይ ተሰምቶት ነበር፣ እናም የበለጠ ጸለየ። ላቡ መሬት ላይ የሚወድቅ የደም ጠብታዎች ነበሩ።

ማቴዎስ 26፥42ሉቃስ 22፥43–44ሞዛያ 3፥7ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 19፥16–19

ኢየሱስ ጴጥሮስን፣ ያዕቆብን እና ዮሐንስን ቀሰቀሰ።

ኢየሱስ በተጨማሪ ሁለት ጊዜ ወደ ጴጥሮስ፣ ወደ ያዕቆብና ወደ ዮሐንስ ሄዶ ተኝተው አገኛቸው። በመጨረሻም ቀሰቀሳቸው፣ ምክንያቱም የሚወሰድበት ጊዜ ደርሱ ነበርና።

ማቴዎስ 26፥43–46