በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ይቅር የማይለው አገልጋይ ምሳሌ—ኢየሱስ ስለይቅርታ አስተማረ


ማቴዎስ 18፥21-34

ይቅር የማይለው አገልጋይ ምሳሌ

ኢየሱስ ስለይቅርታ አስተማረ

ጴጥሮስ ኢየሱስን ጥያቄ ጠየቀው።

አንድ ቀን ጴጥሮስ ኢየሱስን አንድ አስፈላጊ ጥያቄ ጠየቀው። ሰዎች ሃጢያትን ባደረጉ ጊዜ ስንት ጊዜ ይቅር ማለት እንደሚገባው ለማወቅ ፈለገ። ‘’ሰባት ጊዜ?’’ ጴጥሮስ ጠየቀ ኢየሱስም የጴጥሮስን ጥያቄ አንድን ታሪክ ወይም ምሳሌ በመናገር መለሰለት።

ማቴዎስ 18፥15-21

አንድ አገልጋይ የንጉስ ብድር ነበረበት።

በታሪኩ ውስጥ፣ ብዙ አገልጋዮች የነበሩት አንድ ንጉስ ነበር። ከአገልጋዮቹ አንዱ የንጉሱ አስር ሺህ መክሊቶች ነበረበት። ያም ብዙ ገንዘብ ነበር!

ማቴዎስ 18፥23–24

አገልጋዩ ብድሩን ለመክፈል አልቻለም ነበር።

አገልጋዩ ለንጉሱ በጭራሽ ሊከፍለው አልቻለም። ንጉሱም እዳውን ለመክፈል አገልጋዩን እና ቤተሰቦቹን መሸጥ እንዳለበት ተናገረ።

ማቴዎስ 18፥25

አገልጋዩም ይቅርታን ጠየቀ።

አገልጋዩም ይህን በሰማ ጊዜ በጉልበቱ ተንበረከከ። ንጉሱም ተጨማሪ ጊዜን እንዲሰጠው ተማጸነ። ‘’እባክህ ታገሰኝ፣’’ አለው፣ ‘’እና ሁሉንም እከፍልሃለሁ።’’

ማቴዎስ 18፥26

ንጉሱም አገልጋዩን ይቅር አለው።

ንጉሱም ለአገልጋዩ ራራለት። እርሱም ይቅር ሊለው ወሰነ። አገልጋዩ ገንዘቡን መክፈል አላስፈለገውም። እዳውም ተትቶለት በነጻ ሄደ!

ማቴዎስ 18፥27

አገልጋዩ ከሌላ ሰው ገንዘብን በእዳ ይጠይቅ ነበር።

ከዚያም አገልጋዩ ትንሽ ለእርሱ የገንዘብ እዳ ያለበትን አንድ ሰው አገኘ። ሰውየውንም አንቆ ይዞ ‘’ክፈለኝ’’ አለው።

ማቴዎስ 18፥28

ሰውየውም አገልጋዩን ይቅርታ ጠየቀ።

ሰውየው በጉልበቱ ተንበረከከ። ‘’እባክህ ታገሰኝ፣’’ አለው፣ ‘’እና ሁሉንም እከፍልሃለሁ።’’ ነገር ግን አገልጋዩ ይቅር ሊለው አልወደደም። ወደ ወህኒ ላከው።

ማቴዎስ 18፥29-30

ንጉሱ ለአገልጋዩ ስለ ይቅርታ ነገረው።

ንጉሱም የሆነውን በሰማ ጊዜ፣ አገልጋዩን ሊያየው ጠየቀ። ንጉሱ ለአገልጋዩ ትልቅ እዳ እንደተወለት እና ይቅር እንዳለው አስታወሰው። ንጉሱ ለአገልጋዩ ብዙ ገንዘብ የነበረበትን እርሱን ይቅር እንዳለው ነገረው።

ማቴዎስ 18፥31–33

ኢየሱስ ስለ ይቅርታ ከጴጥሮስ ጋር ሲነጋገር።

ሁላችንም ለራሳችን ልንከፍለው የማንችለው እዳ አለብን። ኢየሱስ ለጴጥሮስ እግዚአብሔር ይቅር ስላለን ሌሎችን እንዲሁ ይቅር ማለት እንዳለብን ገለጸ። እናም ከሰባት ጊዜ በኋላ ማቆም እንደሌለብን ነገር ግን ሁል ጊዜ ይቅር ለማለት ፈቃደኛ መሆን አለብን።

ማቴዎስ 18፥22፣ 34-35; እንዲሁም ማቴዎስ 6፥14ትምህርት እና ቃልኪዳኖች 64፥9–10ተመልከቱ።