ማቴዎስ 18፥21-34
ይቅር የማይለው አገልጋይ ምሳሌ
ኢየሱስ ስለይቅርታ አስተማረ
አንድ ቀን ጴጥሮስ ኢየሱስን አንድ አስፈላጊ ጥያቄ ጠየቀው። ሰዎች ሃጢያትን ባደረጉ ጊዜ ስንት ጊዜ ይቅር ማለት እንደሚገባው ለማወቅ ፈለገ። ‘’ሰባት ጊዜ?’’ ጴጥሮስ ጠየቀ ኢየሱስም የጴጥሮስን ጥያቄ አንድን ታሪክ ወይም ምሳሌ በመናገር መለሰለት።
ማቴዎስ 18፥15-21
በታሪኩ ውስጥ፣ ብዙ አገልጋዮች የነበሩት አንድ ንጉስ ነበር። ከአገልጋዮቹ አንዱ የንጉሱ አስር ሺህ መክሊቶች ነበረበት። ያም ብዙ ገንዘብ ነበር!
ማቴዎስ 18፥23–24
አገልጋዩ ለንጉሱ በጭራሽ ሊከፍለው አልቻለም። ንጉሱም እዳውን ለመክፈል አገልጋዩን እና ቤተሰቦቹን መሸጥ እንዳለበት ተናገረ።
ማቴዎስ 18፥25
አገልጋዩም ይህን በሰማ ጊዜ በጉልበቱ ተንበረከከ። ንጉሱም ተጨማሪ ጊዜን እንዲሰጠው ተማጸነ። ‘’እባክህ ታገሰኝ፣’’ አለው፣ ‘’እና ሁሉንም እከፍልሃለሁ።’’
ማቴዎስ 18፥26
ንጉሱም ለአገልጋዩ ራራለት። እርሱም ይቅር ሊለው ወሰነ። አገልጋዩ ገንዘቡን መክፈል አላስፈለገውም። እዳውም ተትቶለት በነጻ ሄደ!
ማቴዎስ 18፥27
ከዚያም አገልጋዩ ትንሽ ለእርሱ የገንዘብ እዳ ያለበትን አንድ ሰው አገኘ። ሰውየውንም አንቆ ይዞ ‘’ክፈለኝ’’ አለው።
ማቴዎስ 18፥28
ሰውየው በጉልበቱ ተንበረከከ። ‘’እባክህ ታገሰኝ፣’’ አለው፣ ‘’እና ሁሉንም እከፍልሃለሁ።’’ ነገር ግን አገልጋዩ ይቅር ሊለው አልወደደም። ወደ ወህኒ ላከው።
ማቴዎስ 18፥29-30
ንጉሱም የሆነውን በሰማ ጊዜ፣ አገልጋዩን ሊያየው ጠየቀ። ንጉሱ ለአገልጋዩ ትልቅ እዳ እንደተወለት እና ይቅር እንዳለው አስታወሰው። ንጉሱ ለአገልጋዩ ብዙ ገንዘብ የነበረበትን እርሱን ይቅር እንዳለው ነገረው።
ማቴዎስ 18፥31–33
ሁላችንም ለራሳችን ልንከፍለው የማንችለው እዳ አለብን። ኢየሱስ ለጴጥሮስ እግዚአብሔር ይቅር ስላለን ሌሎችን እንዲሁ ይቅር ማለት እንዳለብን ገለጸ። እናም ከሰባት ጊዜ በኋላ ማቆም እንደሌለብን ነገር ግን ሁል ጊዜ ይቅር ለማለት ፈቃደኛ መሆን አለብን።
ማቴዎስ 18፥22፣ 34-35; እንዲሁም ማቴዎስ 6፥14፤ ትምህርት እና ቃልኪዳኖች 64፥9–10ተመልከቱ።