በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ኢየሱስ ሕይወቱን ለእኛ አሳልፎ ሰጠ—ከኃጢአት እና ከሞት ለማዳን መስዋዕት ሆነ


ማቴዎስ 27ሉቃስ 23ዮሐንስ 19

ኢየሱስ ሕይወቱን ለእኛ አሳልፎ ሰጠ

ከኃጢአት እና ከሞት ለማዳን መስዋዕት ሆነ

ወታደሮች በኢየሱስ ራስ ላይ የእሾህ አክሊል ደፉበት።

ጲላጦስ ኢየሱስ እንዲሰቀል ከወሰነ በኋላ ለወታደሮቹ ኢየሱስን እንዲወስዱት ነገራቸው። እነርሱም እርሱን ገረፉት፣ ተፉበት፣ በራሱም ላይ የእሾህ አክሊል ደፉበት፣ እንዲሁም አፌዙበትም።

ማርቆስ 15፥15–20

ኢየሱስ ከባድ የእንጨት መስቀል ተሸክሞ።

ወታደሮቹ ኢየሱስ ከባድ የእንጨት መስቀል እንዲሸከም አደረጉት። ከኢየሩሳሌም ውጭ ወደምትገኘው ጎልጎታ ወደምትባል ስፍራ ወሰዱት።

ዮሐንስ 19፥17

ወታደሮቹ ኢየሱስን በመስቀል ላይ ቸነከሩት።

ወታደሮቹ የኢየሱስን እጆችና እግሮች በመስቀል ላይ ቸነከሩ። ኢየሱስ የሰማይ አባቱ ወታደሮቹን ይቅር እንዲላቸው ጠየቀ፣ ምክንያቱም የእግዚአብሔርን ልጅ እየሰቀሉ እንደሆነ ስለማያውቁ።

ሉቃስ 23፥33–34፤ በተጨማሪም የጆሴፍ ስሚዝ ትርጉም የግርጌ ማስታወሻ 34c ተመልከቱ።

ብዙ ሰዎች ኢየሱስንና ሁለት ወንጀለኞችን ሲሰቀሉ እየተመለከቱ።

በዚያን ቀን ሁለት ወንጀለኞች ከኢየሱስ ጋር ተሰቅለው ነበር። ከእነርሱም አንዱ፣ “አንተስ ክርስቶስ አይደለህምን? ራስህንም እኛንም አድን” አለው።

ሉቃስ 23፥39

ኢየሱስ ከወንጀለኞቹ አንዱ ጋር ተነጋገረ።

ሌላው ወንጀለኛም ለእነርሱ ቅጣታቸው ይገባቸዋል፣ ኢየሱስ ግን ምንም ጥፋት አልሠራም አለ። ኢየሱስንም በመንግሥቱ እንዲያስበው ጠየቀው። ኢየሱስ በቅርቡ በመንፈስ ዓለም አብረው እንደሚሆኑ ነገረው።

ሉቃስ 23፥40–43

ኢየሱስ ዮሐንስን እናቱን እንዲንከባከብ ነገረው።

ኢየሱስ ክርስቶስን የተከተሉ ብዙ ሴቶች ከእርሱ ጋር ለመሆን ወደ መስቀል መጥተው ነበር። ከሴቶቹ አንዷ የኢየሱስ እናት ማርያም ነበረች። ኢየሱስም እርሷን አየ እናም ከሐዋርያቱ አንዱ የሆነውን ዮሐንስ እንዲንከባከባት ነገረው።

ዮሀንስ 19፥25–27፤ ደግሞም ሉቃስ 8፥1–3ማርቆስ 15፥40–41 ተመልከቱ።

ጨለማ ምድሪቱን ሸፈነ።

ለሦስት ሰዓታት ያህል ጨለማ ምድሪቱን ሸፈነ። ኢየሱስ በጣም ብቸኝነት ተሰማው። የሰማይ አባቱ እንደተወው ተሰማው።

ማቴዎስ 27፥45–46

ኢየሱስ ሕይወቱን አሳልፎ ሰጠ።

በመጨረሻም ኢየሱስ መከራውን እንደጨረሰ አወቀ። እርሱም፣ “አባት ሆይ፤ ተፈጸመ፤ ፈቃድህም ተፈጸመ” አለ። ከዚያም ኢየሱስ አንገቱን ደፍቶ ሕይወቱን አሳልፎ ሰጠ። በእውነት መሞቱን ለማየት አንድ ወታደር ጎኑን በጦር ወጋው።

የጆሴፍ ስሚዝ ትርጉም፣ ማቴዎስ 27፥54 (በማቴዎስ 27፥50፣ የግርጌ ማስታወሻ a)፤ ዮሐንስ 19፥28–30፣ 34 ተመልከቱ።

የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ለሁለት ተቀደደ።

ኢየሱስ ሲሞት፣ ምድርም ተናወጠች። ዓለቶችም ተሰነጠቁ። የቤተመቅደሱ መጋረጃ፣ በቤተመቅደሱ ውስጥ የተቀደሰውን ቦታ የሚሸፍነው መጋረጃ፣ ለሁለት ተቀደደ።

ማቴዎስ 27፥51

ኢየሱስን የሚመለከቱ ወታደሮች ፈሩ።

ወታደሮቹ ፈሩ። እነርሱም፣ “ይህ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነበር” አሉ።

ማቴዎስ 27፥54

የኢየሱስ እናትና ደቀ መዛሙርቱ አስከሬኑን በመቃብር ውስጥ አስቀመጡት።

የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አስከሬኑን በጨርቅ ጠቅልለው በአትክልት ስፍራ ውስጥ ባለው መቃብር ውስጥ አስቀመጡት። በኋላም በመቃብሩ በር ፊት ለፊት አንድ ትልቅ ድንጋይ አንከባለሉ።

ማቴዎስ 27፥57–61ዮሐንስ 19፥38–41