በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
መልአክ ጴጥሮስን ከእስር ቤት አወጣው— እግዚአብሔር ጸሎቶችን ይመልሳል


የሐዋርያት ስራ 12፥1–17

መልአክ ጴጥሮስን ከእስር ቤት አወጣው

እግዚአብሔር ጸሎቶችን ይመልሳል

ጴጥሮስ በእስር ቤት ሲጣል።

ሄሮድስ የተባለ ንጉሥ ክርስቲያኖችን አይወድም ነበር። ሐዋርያው ያዕቆብን ገደለው። ከዚያም ጴጥሮስን ወደ እስር ቤት አስገባው። እስር ቤቱን እንዲጠብቁ 16 ወታደሮችን አስቀመጠ።

የሐዋርያት ስራ 12፥1–4

ሰዎች ስለ ጴጥሮስ እየጸለዩ።

የቤተክርስቲያኗ አባላት ይህን በሰሙ ጊዜ ስለ ጴጥሮስ ወደ ሰማይ አባት ጸለዩ።

የሐዋሪያት ስራ 12፥5

ጴጥሮስ እስር ቤት ውስጥ ተኝቶ።

አንድ ምሽት፣ ጴጥሮስ ተኝቶ ነበር። በሁለት ወታደሮች መካከል በሁለት ሰንሰለት ታስሮ ነበር።

የሐዋሪያት ስራ 12፥6

አንድ መልአክ ለጴጥሮስ ተገለጠለት።

ድንገት በእስር ቤቱ ውስጥ ብርሃን በራ እንዲሁም አንድ መልአክ ታየ። መልአኩም “ፈጥነህ ተነስ” አለን እናም ሰንሰለቶቹም ከጴጥሮስ እጅ ወደቁ። መልአኩም ጴጥሮስን እንዲከተለው ነገረው።

የሐዋርያት ስራ 12፥7–8

መልአኩ ጴጥሮስን ከዘበኞቹ አሻግሮ ወሰደው።

ጴጥሮስም እያለመ እንደሆነ አሰበ። መልአኩን በመከተል ዘበኞቹን አልፎ ሄደ። ወደ ከተማይቱ የሚወስደው የብረት በር በራሱ ተከፈተ፤ ጴጥሮስና መልአኩም በእርሱ ውስጥ አለፉ።

የሐዋርያት ስራ 12፥9–10

ጴጥሮስ ብቻውን በከተማ ውስጥ ሲሄድ።

መልአኩ ሄደ፤ ጴጥሮስም እያለመ እንዳልሆነ ተገነዘበ። ጌታ ሊያድነው መልአኩን እንደላከ አወቀ።

የሐዋርያት ስራ 17፥10–11

ጴጥሮስም የማርያምን ቤት በር አንኳኳ።

ጴጥሮስ ማርያም ወደምትባል አንዲት ሴት ቤት ሄደ፤ በዚያም ብዙ የቤተክርስቲያን አባላት ለመጸለይ መጥተው ነበር። በሩን አንኳኳ።

የሐዋርያት ስራ 12፥22–13

ሮዴ የጴጥሮስን ድምፅ ከበሩ ጀርባ ሰማች።

ሮዴ የተባለች ሴት ወደ በሩ መጣች። የጴጥሮስን ድምፅ ስትሰማ በጣም ተደሰተች! ለሌሎቹ ለመንገር ሮጠች።

የሐዋርያት ስራ 12፥13–14

ሮዴ ጴጥሮስ በሩ ላይ እንዳለ ለቤተክርስቲያኗ አባላት ነገረቻቸው።

ሮዴ ጴጥሮስ በሩ ላይ እንዳለ ለሁሉም ስትነግራት አላመኗትም። ጴጥሮስ ማንኳኳቱን ቀጠለ።

የሐዋርያት ስራ 12፥15–16

ጴጥሮስ ጌታ ከእስር ቤት እንዳወጣው ለቤተክርስቲያኗ አባላት ነገራቸው።

በመጨረሻም በሩን ከፍተው እውነት መሆኑን አዩ። ጴጥሮስ ደህና ነበር! ጌታ ጸሎታቸውን መለሰላቸው። ጴጥሮስም ጌታ ከእስር ቤት እንዴት እንዳወጣው ለሁሉም ተናገረ።

የሐዋርያት ስራ 12፥16–17