ማቴዎስ 25፥31–46
“ለእኔ አደረጋችሁት”
ሌሎችን ስናገለግል፣ ኢየሱስን እያገለገልን ነን
ኢየሱስ ክርስቶስ ወደአባቱ ከተመለሰ በኋላ፣ ወደምድር ከሁሉም ቅዱስ መላእክት ጋር ተመልሶ እንደሚመጣ ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው። አንድ ቀን፣ ከሁሉም ሀገራት የመጡ ህዝብ በፊቱ ይሰበሰባሉ—የተከተሉትም ሆነ ያልተከተሉት ህዝብ።
ማቴዎስ 25፥31–33
ኢየሱስ የሚከተሉትን ህዝብ በተራበበት ጊዜ ስለመገቡት ወደ መንግስቱ መግባት እንደሚችሉ ነገራቸው። ሲጠማው፣ የሚጠጣውን ሰጥተውት ነበር።
ማቴዎስ 25፥34–35
በሚያስፈልገውም ጊዜ ልብስ እናም የሚቆይበት ቦታ ሰጡት። ሲታመም ወይም ሲታሰር፣ እርሱን ጎበኙት።
ማቴዎስ 25፥36
ህዝቡም ኢየሱስን እነዚህን አይነት ደግ ነገሮች መቼ እንዳደረጉለት ይጠይቁታል። አዳኙም ለሌሎች ሰዎች መልካም ነገር ስናደርግ፣ መልካም ነገርን ለእርሱ እያደረግን እንደሆነ ያስረዳል።
ማቴዎስ 25፥37–40
ኢየሱስ ላልተከተሉት ህዝቦች መንግስቱ ውስጥ መግባት እንደማይችሉ ይናገራል። ሲርበው እና ሲጥመው ምግብም ሆነ መጠጥ አልሰጡትም።
ማቴዎስ 25፥41–42
ልብስ ወይም የሚቆይበት ቦታ ሲያስፈልገው እነርሱ አልረዱትም። ሲታመም ወይም ሲታሰር፣ እርሱን አልጎበኙትም።
ማቴዎስ 25፥43
ኢየሱስም እርዳታ የሚያስፈልገውን ለመርዳት ስንመርጥ፣ እርሱን ለመርዳት እንዳልመረጥን ገለጽ። ሌሎችን ለመርዳት ስንመርጥ፣ ኢየሱስን ለመርዳት እየመረጥን ነን።
ማቴዎስ 25፥45