ዮሀንስ 21፤ ማቴዎስ 28፥16–20፤ ማርቆስ 16፥15–19
ኢየሱስ ሐዋሪያቱ በጎቹን እንዲመግቡ ጠየቀ
ሌሎችን ስለእርሱ በማስተማር ለኢየሱስ ፍቅርን ማሳየት
ኢየሱስ ከሞት ከተነሳ በኋላ፣ ጴጥሮስ እና አንዳንድ ሌሎች ሐዋሪያት አሳ ለማጥመድ ሄዱ። ምንም እንኳን ምሽቱን በሙሉ አሳ ቢያጠምዱም፣ ምንም አላገኙም።
ዮሀንስ 21፥1–3
በሚቀጥለው ቀን ጠዋት፣ ሐዋሪያቱ ኢየሱስን በባህር ዳር ላይ አዩት፣ ነገር ግን እርሱ እንደሆነ አላወቁም። አሳ እንዳጠመዱ ጠየቃቸው። አላጠመድንም አሉት።
ዮሀንስ 21፥4–5
ኢየሱስም ሐዋሪያት መረቡን በታንኳይቱ በስተቀኝ እንዲጥሉት እና አሳ እንደሚያገኙ ነገራቸው። ሐዋሪያት ኢየሱስ እንዳለው አደረጉ፣ እና፣ ከአንድ መቶ በላይ አሳዎች መረቡን ሞሉ። መረቡ በአሳ ተሞልቶ ከባድ ስለነበር ሐዋሪያቱ ወደ መርከቡ ጎትተው ሊያስገቡት አልቻሉም።
ዮሀንስ 21፥6
ከዚያም ዮሀንስ ሰውየው ማን እንደሆነ አወቀ። ለጴጥሮስም “ጌታ እኮ ነው” አለው። ጴጥሮስ ወደ ባህሩ ዘለለ እናም ወደ ኢየሱስ ዋኘ። ሌሎቹ ሐዋሪያት መርከቡን እና አሳዎቹን ወደ ባህር ዳር አመጡት። ኢየሱስ ዳቦ እና አሳ እየጠበሰ ነበር፣ እንዲሁም ሐዋሪያት ከእርሱ ጋር እንዲበሉ ጋበዛቸው።
የዮሀንስ ወንጌል 21፥7–13
ከበሉ በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስን “ከእነዚህ ይልቅ ትወደኛለህን?” አለው። ጴጥሮስም አዎን አለ። ከዚያም ኢየሱስ “ግልገሎቼን አሰማራ”
ዮሐንስ 21፥15
ከዚይም ኢየሱስ ጴጥሮስን ትወደኛለህ ብሎ ጠየቀው። እንደገናም፣ ጴጥሮስ አዎን አለ። ኢየሱስም “ጠቦቶቼን ጠብቅ” አለው
ዮሀንስ 21፥16
ኢየሱስ ጴጥሮስን ለሶስተኛ ጊዜ ትወደኛለህ ብሎ ጠየቀው። ጴጥሮስም “ጌታ ሆይ፥ አንተ ሁሉን ታውቃለህ፤ እንድወድህ አንተ ታውቃለህ” አለው። ኢየሱስም እንደገና “በጎቼን አሰማራ” አለው። ጴጥሮስ እርሱን የሚከተሉትን ሰዎች እንዲንከባከብ ፈልጎ ነበር።
ዮሀንስ 21፥17
በኋላም፣ ኢየሱስ ሐዋሪያቱ ከእርሱ ጋር በተራራ ላይ እንዲገናኙ ጠየቃቸው። በዚያም ወንጌሉን ለአለም ሁሉ እንዲካፈሉ፣ ለሰዎች ትእዛዛቱን እንዲያስተምሩ፣ እና የሚያምኑትን ሁሉ እንዲያጠምቁ ነገራቸው። “ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” አላቸው። ከእነርሱ ጋር እንደሚገኝ እንዲሁም በመንፈስ ቅዱስ በኩል ሀይል እንደሚሰጣቸው ቃል ገባላቸው።
ማቴዎስ 28፥16–20፤ ማርቆስ 16፥15–19፤ የሐዋሪያት ስራ 1፥8
ከዚያም ኢየሱስ ወደ ሰማይ በዳመና ላይ አረገ። ወደ ሰማይ አባቱ ተመለሰ። ሐዋሪያት እርሱ ሲሄድ እየተመለከቱ ሳሉ፣ ሁለት መላእክት መጡ። ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሄዷል፣ አንድ ቀን በዚህ መንገድ ወደ ምድር እንደገና ይመለሳል አሏቸው።
የሐዋሪያት ስራ 1፥9–11