ማቴዎስ 26፤ ሉቃስ 22፤ ዮሀንስ 13–14
የመጨረሻው እራት
ኢየሱስ ቅዱስ ቁርባንን አስተዋወቀ
ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ የአይሁድ ፋሲካን ለማክበር ኢየሩሳሌም ውስጥ ነበሩ። የአይሁድ ህዝብ ፋሲካን በየአመቱ ያከብሩ ነበር። ይህም ከብዙ አመታት በፊት ቤተሰቦቻቸው በግብጽ ውስጥ ባሪያዎች እንደነበሩ እና እግዚአብሔር እንዲያመልጡ እንደረዳቸው ለማስታወስ ይረዳቸው ነበር።
ዘፀአት 12፤27
በኢየሩሳሌም ውስጥ እያሉ፣ ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ አብረው ልዩ ግብዣ አደረጉ። ኢየሱስ ይህን ግብዣ ከእነርሱ ጋር ለመካፈል በጉጉት ይጠብቅ ነበር።
ሉቃስ 22፥7–15
መብላት ከጨረሱ በኋላ፣ ኢየሱስ በመታጠቢያው ውስጥ ውኃ ጨመረ። የሐዋሪያቱን እግሮች ማጠብ ጀመረ።
ዮሀንስ 13፥4–5
የጴጥሮስ ተራ ሲደርስም፣ ኢየሱስ ይህን ለምን እንደሚያደርግ ጠየቀው። እግርን ማጠብ ሰራተኞች ብቻ የሚያደርጉት ነገር ነበር።
ዮሀንስ 13፥6
ኢየሱስ እግራቸውን የሚያጥበው ለእነርሱ ምሳሌ ለማሳየት እንደሆነ ነገራቸው። እነርሱን እንደወደዳቸው እርስ በርስ እንዲያገለግሉ እና እንዲዋደዱ ፈልጎ ነበር። ይህን ካደረጉ፣ ሰዎች የእርሱ ደቀ መዛሙርት እንደሆኑ ያውቃሉ።
ዮሀንስ ወንል 13፥14–16፣ 34–35
ኢየሱስ በቅርብ እንደሚሞት ለደቀ መዛሙርቱ ነገራቸው። ጴጥሮስ ለኢየሱስ ለመሞት ፈቃደኛ ነኝ አለ።
ዮሀንስ 13፥36–38
ነገር ግን ኢየሱስ አስቸጋሪ ጊዜያት እንደሚመጡ ያውቅ ነበር። እርሱም ጴጥሮስ በሚቀጥለው ቀን ጠዋት ዶሮ ከመጮሁ በፊት ኢየሱስን አላውቅም እንደሚል ለጴጥሮስ ነገረው።
ዮሀንስ 13፥38
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ እንደሚጨነቁ እና እንደሚፈሩ አውቆ ነበር። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን እንደሚልክላቸው ቃል ገባላቸው። መንፈስ ቅዱስ ያጽናናቸዋል፣ ያስተምራቸዋል፣ እንዲሁም ኢየሱስ ክርስቶስ ምን እንዳስተማራቸው ለማስታወስ ይረዳቸዋል። እንዳይጨነቁ ወይም እንዳይፈሩ ነገራቸው። እንዲህም አለ፣ “ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ።”
ዮሀንስ 14፥1፣ 15–16፣ 26–27
ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ ሁልጊዜም እንዲያስታውሱት የሚረዳ በጣም ልዩ ነገር አደረገ። ቅዱስ ቁርባንን ሰጣቸው። መጀመሪያ፣ ዳቦውን ባረከ፣ ቆራረጠው፣ እናም ለሐዋሪያቱ ሰጠ። ኢየሱስም ዳቦውን በሚበሉበት ጊዜ ስለ አካሉ እንዲያስቡ ነገራቸው። ለእነርሱ እንደሚሞት እንዲያስታውሱም ጠየቃቸው።
ማቴዎስ 26፥26፤ ሉቃስ 22፥19
ኢየሱስ ወይኑን በጽዋ ውስጥ ቀዳው። ወይኑን ባረከው እና ሐዋሪያቱ እንዲጠጡት ነገራቸው። ኢየሱስም ወይኑን በሚጠጡበት ጊዜ ስለ ደሙ እንዲያስቡ ነገራቸው። እኛ ንስሀ ለመግባት እና ይቅርታ ለመጠየቅ እንችል ዘንድ እርሱ ለሁሉም ሰዎች ህመም እና ኃጢያቶች እንደሚሰቃይ፣ እንደሚደማ እና እንደሚሞት እንዲያስታውሱ ጠየቃቸው።
ማቴዎስ 26፥27–28፤ ሉቃስ 22፥20
ከዚያም ኢየሱስ እርሱ እንደ ወይን ግንድ፣ ደቀ መዛሙርቱ ደግሞ እንደ ቅርንጫፎች እንደሆኑ አስረዳ። ቅርንጫፉ ከወይን ግንድ ጋር ተገናኝቶ ከቆየ፣ ፍሬ ያፈራል። ቅርንጫፉ ከወይን ግንድ ጋር ተገናኝቶ ካልቆየ፣ ይሞታል እናም ፍሬ አያፈራም። ኢየሱስ ደቀ መዛሙርቱ እርስ በርስ በመዋደድ እና ትእዛዛቱን በመጠበቅ ሁልጊዜ ከእርሱ ጋር ቅርብ ሆነው እንዲቆዩ ፈልጓል።
ዮሀንስ 15፥4–12
እነዚህን ነገሮች ካስተማረ በኋላ፣ ኢየሱስ እና ሐዋሪያቱ መዝሙር ዘመሩ። ጌቴሴማኒ ወደሚባል የአትክልት ስፍራም ሄዱ።
ማቴዎስ 26፥30