በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ጳውሎስ ሰውነታችንን ከቤተመቅደስ ጋር ያነጻጽራል—ከእግዚአብሔር የመጡ የተቀደሱ ስጦታዎች


1 ቆሮንቶስ 6፥16–20

ጳውሎስ ሰውነታችንን ከቤተመቅደስ ጋር ያነጻጽራል

ከእግዚአብሔር የመጡ የተቀደሱ ስጦታዎች

ጳውሎስ በቆሮንቶስ ስለኢየሱስ እያስተማረ።

ቆሮንቶስ በባህር አጠገብ የነበረች ትልቅ ከተማ ነበረች። ከተማዋ እግዚአብሔርን የማያመልኩ ብዙ ሰዎች የነበሩባት ነበረች። ጳውሎስ በቆሮንቶስ ለነበሩ ሰዎች ስለኢየሱስ አስተማረ። ብዙ ሰዎች አምነው ተጠመቁ።

የሐዋርያት ስራ 18፥8–11

አንዳንድ ሰዎች ትእዛዛትን አያከብሩም ነበር።

ጳውሎስ ከሄደ በኋላ፣ የቤተክርስቲያኗ አባላት አንዳንድ ችግሮች እንደነበሩባቸው ሰማ። ብዙ ሰዎች በቆሮንቶስ ሰውነታችንን እንዴት መያዝ እና መጠቀም እንዳለብን በሚመለከት የእግዚአብሔርን ትእዛዛት አያከብሩም ነበር።

1 ቆሮንቶስ 6፥13–18

ጳውሎስ ሰውነታችን እንደቤተመቅደስ መሆኑን የሚገልጽ ደብዳቤ እየጻፈ።

ጳውሎስ ደብዳቤ ጻፈላቸው። ሰውነታችን እንደ እግዚአብሔር ቤተመቅደስ እንደሆነ ተናገረ። ቤተመቅደስ የእግዚአብሔር ቤት በመሆኑ በአክብሮት እንጠብቀዋለን። ሰውነታችንም እንዲሁ የእግዚአብሔር ስጦታ ስለሆነ በአክብሮት እንይዘዋለን።

1 ቆሮንቶስ 6፥19–20

ቤተሰብ በአንድ ላይ።

የሠማይ አባታችን በሰውነታችን ላይ መልካም ነገሮችን ለማድረግ እንድንመርጥ ይፈልጋል። ይህን ባደረግን ጊዜ፣ መንፈስ ቅዱስ ሁል ጊዜ ከእኛ ጋር ሊኖር ይችላል።

1 ቆሮንቶስ 6፥19

ቤተሰብ ስለኢየሱስ ክርስቶስ የኃጢያት ክፍያ እየተነጋገሩ። ጳውሎስ ከፊት ለፊት እየታየ።

ኢየሱስ ክርስቶስ በስቃዩ ለእኛ ዋጋ እንደከፈለ ተናገረ። ስለ ሰውነታችን መልካም ነገሮችን ስንመርጥ እና የእርሱን ትአዛዛት ስንጠብቅ ለኢየሱስ ያለንን ፍቅር እናሳያለን። ሰውነታችንን እንደቤተመቅደስ በመያዝ ለእግዚአብሔር ስለመልካም ስጦታው አመስጋኞች መሆናችንን እናሳያለን።

1 ቆሮንቶስ 6፥20