በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ኢየሱስ ተጠመቀ—ለእግዚአብሔር ታማኝ የመሆኑን ምሳሌ ማሳየት


ማቴዎስ 3

ኢየሱስ ተጠመቀ

ለእግዚአብሔር ታማኝ የመሆኑን ምሳሌ ማሳየት

የመጥምቁ ዮሐንስ ስዕል።

ሰዎች ለሚመጣው ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲዘጋጁ ለመርዳት እግዚአብሔር ዮሀንስን ሀላፊነት ሰጠው። ዮሐንስ ሰዎችን ንስሐ እንዲገቡ እና እንዲጠመቁ አስተማራቸው። ሰዎችም መጥምቁ ዮሐንስ በማለት ጠሩት።

ማቴዎስ 3፥1–12

ኢየሱስ ክርስቶስ ለመጠመቅ ወደ ዮሐንስ መጣ።

ዮሐንስ ሃያል መምህር ነበር። አያሌ ሰዎች እርሱን ለመስማት እና ለመጠመቅ መጡ። አንድ ቀን ኢየሱስ ሊጠመቅ መጣ።

ማቴዎስ 3፥5፣ 13

ኢየሱስ እና ዮሐንስ ሲነጋገሩ።

ኢየሱስ ዘወትር ለእግዚአብሔር ታዛዥ እንደነበር ዮሐንስ ያውቅ ነበር። ንሰሃ መግባት አላስፈለገውም። ዮሐንስ ኢየሱስን ማጥመቅ እንደሚገባው አላመነም። ዮሐንስ ራሱ በኢየሱስ መጠመቅ እንደሚገባ አሰበ።

ማቴዎስ 3፥14

ዮሀንስ ኢየሱስን ሲያጠምቅ።

ኢየሱስ እርሱም መጠመቅ እንደሚያስፈልገው ተናገረ። እርሱ የአባቱን ትዕዛዛት በሙሉ ለማክበር ፈለገ። ለእኛም ምሳሌን ለመተውም ፈለገ። ዮሀንስ ጠመቀው።

ማቲዮስ 3፥ 13–152 ኔፊ 31፥5–7

ኢየሱስ ተጠምቋል። መንፈስ ቅዱስ ወረደ።

ኢየሱስ ከውሃው ከወጣ በኋላ፣ መንፈስ ቅዱስ በእርሱ ላይ በእርግብ አምሳል ወረደ። የሰማይ አባት “የምወደው ልጄ ይህ ነው” በማለት ከሰማይ ተናገረ። የሰማይ አባት በኢየሱስ እጅግ ደስተኛ ነበር።

ማቴዎስ 3፥16–17