ዮሐንስ 11፥1–46
ኢየሱስ አላዛርን ከሞት አስነሳው
’’እኔ ትንሳኤ እና ህይወት ነኝ’’
ማርያም፣ ማርታ፣ እና አልአዛር ቢታንያ በተባለ መንደር ይኖሩ ነበር። በኢየሱስ ክርስቶስ አምነዋል፣ እርሱም ይወዳቸው ነበር። ማርያም እና ማርታ የአልአዛር እህቶች ነበሩ።
ዮሀንስ 11፥1፣ 5
አልዓዛር በጣም ታመመ። ኢየሱስ በሌላ ከተማ ነበር። ማርያም እና ማርታ ኢየሱስ ጓደኛው አልዓዛር እንደታመመ እንዲያውቅ መልእክት ላኩበት።
ዮሐንስ 11፥1-3
ኢየሱስ ለሁለት ቀናት ያህል ቆየ። ከዚያም ለደቀ መዛሙርቱ ወደ ቢታንያ እንደሚሄዱ ነገራቸው፡፡ ደቀመዛሙርቱም ተጨነቁ ምክንያቱም በቢታንያ አካባቢ ያሉ አንዳንድ ሰዎች ኢየሱስን ሊጎዱት ይፈልጉ ነበር። ነገር ግን ኢየሱስ አልአዛርን ለመርዳት ፈልጎ ነበር። ኢየሱስም አልአዛር በዚህ ጊዜ እንደሞተ ተናገረ፣ እናም ከሞት ሊያስነሳው ፈለገ።
ዮሐንስ 11፥6-16
ማርታ ኢየሱስን ከከተማ ውጪ አገኘችው። ኢየሱስ አስቀድሞ መጥቶ ቢሆን ኖሮ አልአዛር አይሞትም ነበር አለች። ኢየሱስ አልአዛር ዳግም መኖር እንደሚችል ቃል ገባ።
ዮሐንስ 11፥17-24
ኢየሱስም፣ “እኔ ትንሳኤ እና ህይወት ነኝ” አለ። እርሱም ማርታን በእርሱ ታምን እንደሆነ ጠየቃት፡፡ እርሷም፣ “አንተ ክርስቶስ መሆንህን እና እግዚአብሔርም ልጅ እንደሆንክ አምናለሁ’’ አለች።
ዮሀንስ 11፥25-27።
ማርታ ወደ ቤቷ ተመልሳ ሄደች እናም ኢየሱስ እንደመጣ ለማርያም ነገረቻት። ስለወንድሟ እያለቀሰች ማርያም መጥታ በኢየሱስ እግር ላይ ወደቀች። ኢየሱስም አለቀሰ። አልአዛርን፣ ማርያምን እና ማርታን ይወዳቸው ነበር።
ዮሐንስ 11፥28-36
ኢየሱስ፣ ማርታ፣ ማርያም፣ እና ሌሎችም አልአዛር ወደተቀበረበት መቃብር ሄዱ። ታላቅም ድንጋይ መቃብሩን ሸፍኖት ነበር። ኢየሱስም ድንጋዩን እንዲያነሱት ነገራቸው።
ዮሐንስ 11፥38-39
ነገር ግን ማርታ አልአዛር ከሞተ አራት ቀን እንደሆነው ለኢየሱስ ነገረችው። ኢየሱስ ለማርታ ቃል ስለገባላት ነገር አስታወሳት። በእርሱ እንድታምን ጠየቃት።
ዮሐንስ 11፥39-40
ኢየሱስም ወደ አባቱ ጸለየ። ሁል ጊዜ ስለሚሰማው እግዚአብሔርን አመሰገነ። ኢየሱስ እግዚአብሄር አዳኝ እንዲሆን እንደላከው ህዝቡ እንዲያምኑ ፈለገ። ኢየሱስም “አልዓዛር ሆይ፣ ተነሳ” በማለት ተጣራ።
ዮሐንስ 11፥41-43
አልዓዛርም እየተራመደ ከመቃብሩ ወጣ። እርሱም በተቀበረበት ጨርቅ እና መከፈኛ ተጠቅልሎ ነበር። ኢየሱስም ለህዝቡ እንዲፈቱት ነገራቸው። በዚያ ከነበሩት ብዙዎችም በዚያ ቀን በእውነት ኢየሱስ አዳኝ፣ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ አመኑ።
ዮሐንስ 11፥44–45