በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ኢየሱስ ማዕበሉን ጸጥ አደረገ—ነፋሱ እና ባህሩ ሳይቀር ይታዘዙለታል


ማቴዎስ 8፥23–27ማርቆስ 4፥36–41

ኢየሱስ ማዕበሉን ጸጥ አደረገ

ነፋሱ እና ባህሩ ሳይቀር ይታዘዙለታል

ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ በጀልባ ውስጥ።

አንድ ቀን፣ ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ በገሊላ ባህር በጀልባ እየተጓዙ ነበር። ነፋሱም በጣም ይነፍስ ነበር። በውሃ እስክትሞላ ድረስ ሞገድም ጀልባዋን ያናውጣት ጀመር። ኢየሱስ፣ ይሁን እንጂ፣ የሰላም እንቅልፍ ተኝቶ ነበር።

ማቴዎስ 8፥23–24

ደቀ መዛሙርቱም ኢየሱስን ቀሰቀሱት።

ደቀመዛሙርቱ ፈርተው ነበር። ኢየሱስን ቀሰቀሱት። “ጌታ ሆይ፥ አድነን፣” በማለት ጮሁ። በባህር ውስጥ የሚሰምጡ እንደሆኑ መስሏቸው ነበር።

ማቴዎስ 8፥25

ኢየሱስ ውሃውን ጸጥ እንዲል አዘዘው።

“ ስለ ምን ትፈራላችሁ?” ሲል ኢየሱስ ጠየቀ። እርሱም ለደቀመዛሙርቱ የተሻለ እምነት እንደሚያስፈልጋቸው ነገራቸው። ኢየሱስም ቆሞ ለነፋሱ እና ለሞገዱ እንዲህ አለ፣ “ዝም በል፥ ጸጥ በል።”

ማቴዎስ 8፥26ማርቆስ 4፥39

ደቀ መዛሙርቱ ኢየሱስ ማእበሉን እንዴት ጸጥ ሊያደርግ እንደቻለ ተደነቁ።

በድንገትም ማእበሉ ቆመ፣ እና ባህሩም ጸጥ አለ። ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ ደህና ሆኑ። የኢየሱስ ደቀመዛሙርት ተገረሙ። ምን አይነት ግለሰብ ነፋሱን እና ባህሩን ሊያዝ ይችላል፣ እናም ይታዘዙለታል በማለት ተደነቁ!

ማቴዎስ 8፥26–27