ማቴዎስ 8፥23–27፤ ማርቆስ 4፥36–41
ኢየሱስ ማዕበሉን ጸጥ አደረገ
ነፋሱ እና ባህሩ ሳይቀር ይታዘዙለታል
አንድ ቀን፣ ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ በገሊላ ባህር በጀልባ እየተጓዙ ነበር። ነፋሱም በጣም ይነፍስ ነበር። በውሃ እስክትሞላ ድረስ ሞገድም ጀልባዋን ያናውጣት ጀመር። ኢየሱስ፣ ይሁን እንጂ፣ የሰላም እንቅልፍ ተኝቶ ነበር።
ማቴዎስ 8፥23–24
ደቀመዛሙርቱ ፈርተው ነበር። ኢየሱስን ቀሰቀሱት። “ጌታ ሆይ፥ አድነን፣” በማለት ጮሁ። በባህር ውስጥ የሚሰምጡ እንደሆኑ መስሏቸው ነበር።
ማቴዎስ 8፥25
“ ስለ ምን ትፈራላችሁ?” ሲል ኢየሱስ ጠየቀ። እርሱም ለደቀመዛሙርቱ የተሻለ እምነት እንደሚያስፈልጋቸው ነገራቸው። ኢየሱስም ቆሞ ለነፋሱ እና ለሞገዱ እንዲህ አለ፣ “ዝም በል፥ ጸጥ በል።”
ማቴዎስ 8፥26፤ ማርቆስ 4፥39
በድንገትም ማእበሉ ቆመ፣ እና ባህሩም ጸጥ አለ። ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ ደህና ሆኑ። የኢየሱስ ደቀመዛሙርት ተገረሙ። ምን አይነት ግለሰብ ነፋሱን እና ባህሩን ሊያዝ ይችላል፣ እናም ይታዘዙለታል በማለት ተደነቁ!
ማቴዎስ 8፥26–27