ሮሜ 3፥21–28፤ 5፥1–11፣ 6፥3–6
ለደህንነት በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ መደገፍ
በጸጋው መዳን
ከተለያዩ አከባቢዎች ሰዎች የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን እየተቀላቀሉ ነበሩ። የቤተክርስቲያኗ አባላት ቅዱሳን ተብለው ይጠሩ ነበር።
ሮሜ 1፥7
አንዳንዶቹ ቅዱሳን አሁንም የሙሴን ህግ ይከተሉ የነበሩ አይሁዳውያን ነበሩ። ሌሎቹ ግን አልነበሩም። የሙሴን ህግ ያስፈልጋቸው ይሆን አይሁን በሚል በመካከላቸው አለመስማማት ነበር።
ሮሜ 2፥14–15፤ 23–29
ጳውሎስ ቅዱሳን ይህ ጥያቄ እንደሚኖራቸው ያውቅ ነበር። እርሱም በሮሜ ለነበሩት ቅዱሳን ደብዳቤ ይጽፍላቸው ነበር። የሙሴን ህግ ለመከተል በመሞከር ብቻ ማንም ሰው ሊድን እንደማይችል ነገራቸው። ሁላችንም ሃጢያት ሰርተናል በማለት አብራራ። ለመዳን፣ እያንዳንዱ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ እምነት ሊኖረው እና እርሱንም ሊከተል ይገባዋል።
ሮሜ 3፥20–23
ጳውሎስም እግዚአብሔር ሃጢያታችንን በራሱ ያኖር ዘንድ ልጁን ኢየሱስን እንደላከ አስተማረ። በኢየሱስ ክርስቶስ መስዋአትነት ምክንያት፣ ንስሀ መግባት እና ለኃጢያታች ምህረትን ማግኘት እንችላለን።
ሮሜ 3፥24–31
ጳውሎስ ኢየሱስ ክርስቶስ ይቅርታን እና መልካምን ማድረግ እንችል ዘንድ ጥንካሬን እንደሚሰጠን አስተማረ። ይህ የተወደደ ስጦታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ይባላል፣ እንዲሁም በተስፋ እና በሃሴት ይሞላናል። ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳደረገው ስንጠመቅ፣ እንደ ኢየሱስ ተከታይ በመሆን አዲስ ህይወት እንደምንጀምር ጳውሎስ አስተምሯል።
ሮሜ 5፥1–11፤ 6፥3–6