ማርቆስ 10፧13–16
ኢየሱስ ሕፃናትን ባረከ
’’መንግስተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉት ናትና’’
ኢየሱስ እያስተማረ እያለ፣ አንዳንድ ሰዎች ታዳጊ ሕፃናትን ወደ እርሱ አመጡ። ኢየሱስ ሕፃናቶቹን እንዲባርክላቸው ፈለጉ። የእርሱም ደቀመዛሙርት ሊያስቆሟቸው ሞከሩ።
ማቴዎስ 19፥13፤ ማርቆስ 10፥13
ኢየሱስ ለደቀ መዛሙርቱ ሕፃናትን ወደ እርሱ እንዲያመጧቸው ነገራቸው። ሕፃናት በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ ያሉ መሆናቸውን ተናገረ። እርሱም ማንም ሰው ከእግዚአብሔር ጋር ዳግም ለመኖር የሚሻ ቢሆን፣ እንደ ሕፃናት መሆን እንዳለበት ገለጸላቸው።
ማቴዎስ 19፥14፤ ማርቆስ 10፥14-15
ከዚያም ኢየሱስ ሕፃናትን ወደ እጆቹ አስጠግቶ ባረካቸው።
ማቴዎስ 19፥15፤ ማርቆስ 10፥16