በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ኢየሱስ አይነ ስውሩን ሰው ፈወሰው—በጊዜ ሂደት የሚከሰት ፈውስ


ማርቆስ 8፥22-25

ኢየሱስ አይነ ስውሩን ሰው ሲፈውስ

በጊዜ ሂደት የሚከሰት ፈውስ

ሰዎች አንድን አይነ ስውር ሰው በኢየሱስ እንዲፈወስ ያመጣሉ።

ቤተሳይዳ በተባለ ከተማ ውስጥ፣ ሰዎች አንድን አይነ ስውር ወደ ኢየሱስ አመጡ። ኢየሱስም ማየት ይችል ዘንድ እንዲባርከው ፈለጉ።

ማርቆስ 8፥22

ኢየሱስ ሰውየውን ባረከው።

ኢየሱስም አይነ ስውሩን ሰው እጁን ያዘው፣ እናም ከከተማው ውጪ እንዲሄድ መራው። ከዚያም ኢየሱስ በሰውየው ላይ እጆቹን ጫነ እናም ባረከው።

ማርቆስ 8፥23

አሁን ሰውየው ማየት ይችላል፣ ነገር ግን ሙሉ በሙሉ ሁኔታ አልነበረም።

ኢየሱስም ሰውየው ማየት ይችል እንደሆነ ጠየቀው። ሰውየው ወደ ላይ ተመለከተ። አሁን ሰውየው ማየት ይችላል፣ ነገር ግን በጣም አጥርቶ አልነበረም። ሰውየውም ሰዎች እንደሚንቀሳቀሱ ዛፎች ሆነው እንደሚታዩት ተናገረ።

ማርቆስ 8፥23–24

አሁን ሰውየው አጥርቶ ማየት ቻለ።

ኢየሱስ ሰውየውን ደግሞ ባረከው። በዚህ ጊዜ፣ ወደ ላይ ባየ ጊዜ፣ ሁሉም ነገር የጠራ ነበር። ኢየሱስም ፈወሰው!

ማርቆስ 8:25