ማርቆስ 8፥22-25
ኢየሱስ አይነ ስውሩን ሰው ሲፈውስ
በጊዜ ሂደት የሚከሰት ፈውስ
ቤተሳይዳ በተባለ ከተማ ውስጥ፣ ሰዎች አንድን አይነ ስውር ወደ ኢየሱስ አመጡ። ኢየሱስም ማየት ይችል ዘንድ እንዲባርከው ፈለጉ።
ማርቆስ 8፥22
ኢየሱስም አይነ ስውሩን ሰው እጁን ያዘው፣ እናም ከከተማው ውጪ እንዲሄድ መራው። ከዚያም ኢየሱስ በሰውየው ላይ እጆቹን ጫነ እናም ባረከው።
ማርቆስ 8፥23
ኢየሱስም ሰውየው ማየት ይችል እንደሆነ ጠየቀው። ሰውየው ወደ ላይ ተመለከተ። አሁን ሰውየው ማየት ይችላል፣ ነገር ግን በጣም አጥርቶ አልነበረም። ሰውየውም ሰዎች እንደሚንቀሳቀሱ ዛፎች ሆነው እንደሚታዩት ተናገረ።
ማርቆስ 8፥23–24
ኢየሱስ ሰውየውን ደግሞ ባረከው። በዚህ ጊዜ፣ ወደ ላይ ባየ ጊዜ፣ ሁሉም ነገር የጠራ ነበር። ኢየሱስም ፈወሰው!
ማርቆስ 8:25