የሐዋርያት ስራ 9፥36–42
ጣቢታ፣ “መልካም ነገር የሞላባት” ሴት
በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ወደ ሕይወት ተመለሰች
ጣቢታ የኢየሱስ ክርስቶስ ታማኝ ደቀ መዝሙር ነበረች። እሷም በባሕር ዳር ኢዮጴ በምትባል ከተማ ትኖር ነበር። ድሆችን ማገልገል እና መርዳት ትወድ ነበር።
የሐዋሪያት ሥራ 9፥36
ጣቢታ ልብስ ሠርታ ለተቸገሩ ሴቶች ሰጠች። ጣቢታን ይወዷት ነበር።
የሐዋርያት ስራ 9፥39
አንድ ቀን ጣቢታ በጠና ታመመች። በጣም ከመታመሟ የተነሳ ሞተች።
የሐዋርያት ስራ 9፥37
በኢዮጴ የነበሩት ሌሎች የቤተክርስቲያን አባላት በጣም አዘኑ። ከኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ የሆነው ጴጥሮስ በአቅራቢያው በሚገኝ ከተማ እንደሚገኝ ያውቁ ነበር። ጴጥሮስን ፈጥኖና ወደ እነርሱ እንዲመጣ እንዲጠይቁት ሁለት ሰዎችን ላኩ።
የሐዋርያት ስራ 9፥38
ጴጥሮስም የጣቢታ ሬሳ ወዳለበት መጣ። ጣቢታ የረዳቻቸው አንዳንድ ሴቶች እዚያ ነበሩ። ለጴጥሮስም የሠራችላቸውን ልብስ አሳዩት።
የሐዋርያት ስራ 9፥39
ጴጥሮስም ሰዎቹ ሁሉ ከክፍሉ እንዲወጡ ጠየቃቸው። ተንበርክኮ ጸለየ።
የሐዋርያት ስራ 9፥40
ጴጥሮስም ከጸለየ በኋላ፣ “ጣቢታ፣ ተነሺ” አላት። ዓይኖን ከፍታ ተቀመጠች ። ጴጥሮስም እንድትቆም ረዳት። እንደገና በህይወት ኖረች! ጴጥሮስም ጓደኞቿ መጥተው እንዲያዩአት ጠራቸው። እነርሱም ተገረሙ! በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል ወደ ሕይወት እንደተመለሰች ያውቁ ነበር። ብዙ ሰዎች በእርሱ አመኑ።
የሐዋርያት ስራ 9፥40–42