ማቴዎስ 12፥1–12፤ ሉቃስ 13፥10–17
ኢየሱስ አንዲትን ሴት በሰንበት ፈወሰ
በተቀደሰ ቀኑ መልካምን ማድረግ
ኢየሱስ እና ደቀመዛሙርቱ በሰንበት ቀን በስንዴ እርሻ መካከል አለፉ። እነርሱም ተርበው ነበር፣ በመሆኑም የተወሰኑ የስንዴ ዘለላዎችን ቀጥፈው በሉ። ፈሪሳውያን የተባሉ አንዳንድ የአይሁድ መሪዎች አዩዋቸው። ፈሪሳውያን ስለሰንበት ቀን አያሌ ህጎችን አውጥተው ነበር። ስንዴን መቀጠፍ የህጋቸው ተቃራኒ ነበር።
ማቴዎስ 12፥1–l2
ፈሪሳውያንም ኢየሱስን ለምን የእርሱ ደቀመዛሙርት ሰንበትን እንደማያከብሩ ጠየቁት። ኢየሱስም ምንም መጥፎ ነገር እንዳላደረጉ መለሰላቸው። እግዚአብሔር የሰንበትን ቀን የሰጠን ህይወታችንን ሊባርክ እንጂ ሊያከብደው አይደለም።
ማቴዎስ 12፥2–8፤ ማርቆስ 2፥27
በኋላም፣ ኢየሱስ በሰንበት ቀን በምኩራብ እያስተማረ ነበር። ኢየሱስ በዚያም አንዲትን ሴት አስተዋለ። ቀጥ ብላ መቆም አልቻለችም ነበር። ለ18 ዓመታት ይህ ችግር ነበረባት።
ሉቃስ 13፥10–12
ኢየሱስ ሴቲቱ ወደ እርሱ እንድትመጣ ጠየቃት። ይባርካትም ዘንድ እጆቹን ጫነባት።
ሉቃስ 13፥12–13
ወዲያውኑም፣ ሴቲቱ ቀጥ ብላ ቆመች። ኢየሱስ በሰንበት ስለፈወሰ የምኩራቡ መሪ ተናደደ።።
ሉቃስ 13፥13–14
ኢየሱስ ይህችን ሴት መርዳት ትክክለኛ ነገር እንደሆነ ተናገረ። በሰንበት መልካምን ማድረግ ትክክለኛ ነገር ነው። መሪውም እፍረት ተሰማው፣ እናም ሴቲቱም በመፈወሷ በምኩራቡ የነበሩ ሰዎች ተደሰቱ።
ሉቃስ 13፥15–17፤ በተጨማሪ ሉቃስ 6፥9 ተመልከቱ።