ሉቃስ 24፥1–12፣ 36–49፤ ዮሀንስ 20
ተነስቷል
ኢየሱስ ክርስቶስ ሞትን ለሁሉም አሸነፈ
የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት ሰውነቱን በመቃብር ውስጥ አስቀመጡ። ሰውነቱን ለመንከባከብ ተጨማሪ ነገሮች ለማድረግ ፈለጉ፣ ነገር ግን ሰንበት ደርሶ ነበር። ከሰበት በኋላ ለመጨረሽ ለመመለስ አቅደው ነበር።
ሉቃስ 23፥52–56
ከኢየሱስ ሞት በሶስተኛው ቀን ጠዋት ላይ፣ መግደላዊት ማርያም እና ሌሎች ወደ መቃብሩ ተመለሱ።
ሉቃስ 24፥1፤ ዮሀንስ 20፥1
በዚያ ሲደርሱም፣ መቃብሩን ሸፍኖ የነበረው ድንጋይ ተፈንቅሎ እንደነበር ተመለከቱ። በመቃብሩ ውስጥ ገቡ፣ እና የኢየሱስ ሰውነት በዚያ አልነበረም።
ሉቃስ 24፥2–3፤ ዮሀንስ 20፥1
ማርያም ለጴጥሮስ እና ዮሀንስ አንድ ሰው የኢየሱስን ሰውነት ወስደዋል ብላ ለመንገር ሮጣ ሄደች። ጴጥሮስ እና ዮሀንስ ወደ መቃብሩ ሮጠው ሲሄዱ።
ዮሀንስ 20፥2–4
ወደ መቃብሩ ሲደርሱ፣ ጴጥሮስ እና ዮሀንስ ወደውስጥ ገቡ። የኢየሱስ ሰውነት እንደሌለ ተመልከቱ። ሰውነቱ ተሸፍኖበት የነበረው ልብስ ኝ በዚያ ነበረ።
ዮሀንስ 20፥5–7
ጴጥሮስ እና ዮሀንስ ወደ ቤት ተመለሱ፣ ግን ማርያም እያለቀሰች በመቃብሩ አጠገብ ቆየች። በመቃብሩ ውስጥ ተመለከተች እና ሁለት መላእክት አየች። እነርሱም ለምን እንደምታለቅስ ጠየቋት። እርሷም አንድ ሰው የኢየሱስን ሰውነት ወስደዋል፣ እናም የት እንዳለ አለውቅም አለች።
ዮሐንስ 20፥11–13
ከዚያም ኢየሱስ መጣ፣ ግን ማርያም እርሱ እንደሆነ አላወቀችም ነበር። ኢየሱስም እንዲህ ብሎ ጠየቃት፣ “አንቺ ሴት፥ ስለ ምን ታለቅሻለሽ?” ማርያም እርሱ የአትክልት ጠባቂ መስሏት ነበር። የኢየሱስ ሰውነት የት እንዳለ እንደሚያውቅ ጠየቀችው።
ዮሀንስ 20፥14–15
ኢየሱስ “ማርያም” አለ። እርሷም ዞር አለች። አሁን እርሱ ኢየሱስ እንደሆነ አወቀች! እርሷም “መምህር ሆይ” አለችው። ኢየሱስ ለሌሎች ደቀ መዛሙርት ወደ ሰማይ አባቱ መፌድ እንደሚያስፈልገው እንድትነግራቸው ጠየቃት። ማርያም ሌሎች ደቀ መዛሙርትን አገኘች እናም ኢየሱስን እንዳየትና እርሱም ዳግም ህያው እንደሆነ ነገረቻቸው።
ዮሀንስ 20፥16–18
በዚያ ምሽት፣ ብዙዎቹ ሐዋሪያት አብረው ተሰብስበው ነበር። የአይሁዶች መሪዎች እነርሱን ለማግኘት እንደሚፈልጉ በመፍራት በሮቹን ዘጉ። በድንገት፣ ኢየሱስ በመካከላቸው ቆሞ አዩት። በመጀመሪያ ፈርተው ነበር። እርሱ መንፈስ መስሏቸው ነበር። ኢየሱስም፣ “ሰላም ለእናንተ ይሁን” አላቸው።
ሉቃስ 24፥33–38፤ ዮሀንስ 20፥19
ኢየሱስ ሐዋሪያት እጆቹን እና እግሮቹን እንዲነኩ ጋበዛቸው። እርሱ መንፈስ ቻ ሳይሆን፣ ሰውነት እንዳለው እንዲያውቆ ፈለገ። ከእነርሱም ጋር አሳ እና የማር ወለላ በላ። ሐዋሪያት እርሱን በማየታቸው በጣም ተደሰቱ!
ሉቃስ 24:39–44፤ ዮሀንስ 20፥20
ከዚያም ኢየሱስ ሐዋሪያቱ ስለሞቱ እና ትንሳኤው ያስተማሩትን ቅዱሳት መጻህፍት እንዲገነዘቡ ረዳቸው። በእርሱ ምክንያት ንስሀ መግባት እና ይቅርታ ማግኘት እንደሚችሉ ለሁሉም እንዲያስተምሩ ፈልጓቸው ነበር። ሐዋሪያት የእርሱ ምስክሮች ይሆናሉ።
ሉቃስ 24፥44–48
ሐዋርያው ቶማስ ኢየሱስ ሲመጣ እዚያ አለነበረም። በእጆቹ ላይ የምስማሩን ምልክት ካላየሁ፣ ኢየሱስ በህይወት መኖሩን አላምንም አለ።
ዮሀንስ 20፥24–25
ከስምንት ቀናት በኋላ፣ ደቀመዛሙርት እንደገና ተሰብስበው ነበር። ኢየሱስ እንደገና መጣ። በዚህ ጊዜ ቶማስ እዚያ ነበር።
ዮሀንስ 20፥26
ኢየሱስ ቶማስ በእጆቹ እና በጎኑ ያሉትን ቁስሎች እንዲነካ ጋበዘው። ቶማስን “ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን” አለው። ቶማስም “ጌታዬ አምላኬም” ብሎ መለሰለት። ቶማስ ኢየሱስ ከሞት እንደተነሳ አሁን አመነ። ኢየሱስም እርሱን ባያዩም የሚያምኑ ሰዎች የተባረኩ ናቸው አለ።
ዮሀንስ 20፥27–29