በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ኢየሱስ በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን መገበ—እርሱ የህይወት እንጀራ ነው


ማቴዎስ 14፥13–21ዮሐንስ 6

ኢየሱስ በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎችን መገበ

እርሱ የህይወት እንጀራ ነው

ኢየሱስ ለብቻው ጊዜን ወሰደ።

መጥምቁ ዮሐንስ እንደተገደለ ኢየሱስ አወቀ። ለብቻው ጊዜ ይኖረው ዘንድ ከከተማ ራቅ ወዳለ ስፍራ ሄደ።

ማቴዎስ 14፥13

ኢየሱስ ከተሰበሰቡ ሰዎች ጋር ሲነጋገር።

ህዝቡም ኢየሱስ ወዴት እንደሄደ ሲያውቁ ይከተሉት ጀመር። ኢየሱስም አያቸው እና ስለእነርሱም ፍቅር አደረበት። ሲባርካቸው እና ሲፈውሳቸው ሙሉ ቀን ፈጀበት።

ማቴዎስ 14፥13–14

ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን ለህዝቡ የሚበላ ነገር እንዲሰጧቸው ጠየቃቸው።

ቀኑም በመሸ ጊዜ፣ ህዝቡ ተራቡ። ደቀመዛሙርቱም ምግብ ያገኙ ዘንድ ህዝቡን ወደከተማ ኢየሱስ መላክ ያለበት መሰላቸው። ነገር ግን ኢየሱስ ባሉበት እንዲሆኑ ፈልጎ ነበር። ኢየሱስ ደቀመዛሙርቱን ለህዝቡ የሚበላ ነገር እንዲሰጧቸው ጠየቃቸው።

ማቴዎስ 14፥15–16

እንድርያስ ከአንድ ብላቴና ትንሽ ምግብ አገኘ።

ሐዋርያው እንድርያስ ለህዝብ የሚሆን አምስት እንጀራ እና ሁለት ትንሽ ዓሣ ያለው ልጅ አገኘ። ነገር ግን፣ ሴቶችን እና ልጆችን ጨምሮ፣ ለመብላት የሚያስፈልጋቸው 5000 ያህል ወንዶች ነበሩ። በዚህች አነስተኛ ምግብ እንዴት የዚህን ያህል ቁጥር ያላቸውን ሰዎች ሊመግቡ ይችላሉ?

ማቴዎስ 14፥17፣ 21ዮሐንስ 6፥8–10

ኢየሱስ ጸለየ እና ምግቡንም ባረከው።

ኢየሱስ ምግቡን ያመጡለት ዘንድ ሐዋርያቱን ጠየቀ። ህዝቡንም እንዲቀመጡ ነገራቸው። ከዚያም ኢየሱስ የሰማይ አባትን ለእንጀራው እና ለዓሳው ለማመስገን እና ለመባረክ ጸሎትን አቀረበ። ከዚያም እንጀራውን እና ዓሳውን ቆራረሰ።

ማቴዎስ 14፥18–19ዮሐንስ 6፥10–11

ሐዋርያቱም ምግቡን ለህዝቡ ሰጡ።

ኢየሱስም እንጀራውን እና ዓሳውን ለህዝቡ እንዲሰጡ ጠየቀ። ሁሉም በሉ እናም ጠገቡ። ከበሉም በኋላ፣ የተረፈው ምግብ 12 መሶብ ሙሉ ነበር።

ማቴዎስ 14፥20ዮሐንስ 6፥11–13

ህዝቡም ተጨማሪ ምግብ ፈልገው ተመልሰው መጡ።

በሚቀጥለው ቀን፣ ህዝቡም ተመልሰው መጡና ኢየሱስን እንደገና አገኙ። ነገር ግን ኢየሱስ ብዙዎቹ የሚከተሉት ምግብ ስለሰጣቸው ብቻ እንደሆነ አወቀ። ኢየሱስ ምግብ ለጥቂት ጊዜ ብቻ የሚቆይ መሆኑን አስታወሳቸው። እርሱ የሚሰጣቸው የተሻለ ነገር አለው።

ዮሐንስ 6፥14፣ 24–27

እርሱ የህይወት እንጀራ እንደሆነ አስተማረ።

ኢየሱስም፣ “እኔ የህይወት እንጀራ ነኝ” አለ። እንጀራ በምድር ህይወትን ይሰጠናል። ነገር ግን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማይ አባት ጋር የዘለዓለምን ህይወት ይሰጠናል።

ዮሐንስ 6፥35–58

ሰዎች በሚያስተምረው ትምህርቱ ተበሳጩ።

አያሌ ሰዎች ኢየሱስ ሊያስተምር እየሞከረ ያለውን ነገር አልወደዱም። ትተውት ሄዱ እናም ኢየሱስን ላለመከተል ወሰኑ።

ዮሀንስ 6፥60፣ 66

ጴጥሮስም ሐዋርያቱ ትተውት እንደማይሄዱ ለኢየሱስ ነገረው።

ከዚያም ኢየሱስ ለሐዋርያቱ፣ “እናንተ ደግሞ ልትሄዱ ትወዳላችሁን?” አላቸው። ጴጥሮስ “ጌታ ሆይ፣ ወደ ማንስ እንሄዳለን? አንተ የዘላለም ህይወት ቃል አለህ” በማለት መለሰለት። ሐዋርያቱ ትተዉት አልሄዱም። እነርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝ እና የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆነ አውቀዋል።

ዮሐንስ 6፥67–69