በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
አንዲት መበለት እና ሁለት ዲናሮች--ኢየሱስ ስለ መስዋእት አስተማረ


ማርቆስ 12፥41–44

አንዲት መበለት እና ሁለት ዲናሮች

ኢየሱስ ስለ መስዋእት አስተማረ

ኢየሱስ ሰዎች በቤተመቅደስ ገንዘብ ሲሰጡ አየ።

ኢየሱስ ወደ ኢየሩሳሌም ቤተመቅደስ ሄደ። በዚያም እያለ፣ ሰዎች ለቤተመቅደስ ስራ ገንዘብ ሲሰጡ ተመለከተ። ባለጠጎች ብዙ ገንዘብ ይሰጡ ነበር።

ማርቆስ 12፥41

የአንዲት ድሃ ሴት ትንሽ ዲናሮች።

ከዚያም አንዲት ድሃ መበለት ሁለት ሳንቲሞችን ሰጠች። በጣምም ብዙ አልነበረም፣ ነገር ግን የነበራት ገንዘብ ሁሉ ያ ነበር።

ማርቆስ 12፥42፣ 44

ሴቲቱ ሁለት ሳንቲሞችን ለገሰች።

ኢየሱስም ሴቲቱን አይቶ ደቀ መዛሙርቱን ጠራቸው እና ያደረገችውን መጥተው እንዲያዩ ጠየቃቸው።

ማርቆስ 12፥43

ኢየሱስ ስለ ሴትየዋ መስዋእት አስተማረ።

ኢየሱስ ሴቲቱ ከሁሉም የበለጠ እንደሰጠች ተናገረ። ባለጠጋ ሰዎች ብዙ ገንዘብ ሰጥተዋል፣ ነገር ግን ከነበራቸው ጥቂቱን ነበር። መበለቷ ትንሽ ገንዘብ ብቻ ነው የሰጠችው፣ ነገር ግን የነበራትን ሁሉ ሰጠች።

ማርቆስ 12፥43-44