አጠቃላይ ጉባኤ
የምህረት እቅድ
የሚያዝያ 2025 (እ.አ.አ) አጠቃላይ ጉባኤ


11:6

የምህረት እቅድ

ጌታ መሀሪ ነው እናም የሰማይ አባታችን የደህንነት ዕቅድ በእውነትም የምህረት እቅድ ነው።

የነቢይ ግብዣ

ባለፈው ሚያዝያ፣ ቤተክርስቲያኗ የከርትላንድን ቤተመቅደስ እንዳገኘች ከተነገረው አስደሳች ዜና በኋላ፣ ፕሬዚዳንት ራስል ኤም. ኔልሰን በ ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 109 ላይ የሚገኘውን የከርትላንድ ቤተመቅደስ ምረቃ ጊዜ የተደረገውን ጸሎት እንድናጠና ጋብዘውን ነበር። ፕሬዚዳንት ኔልሰን የምረቃው ጸሎት፣ “ቤተመቅደስ በእነዚህ የመጨረሻ ቀናት እኔ እና እናንተ የህይወት ፈተናዎችን መቋቋም እንችል ዘንድ መንፈሳዊ ሃይልን” እንዴት እንደሚሠጠን የሚያስተምር ነው” ብለዋል።

የክፍል 109 ጥናታችሁ የባረኳችሁ ግንዛቤዎችን እንዳስገኘላችሁ እርግጠኛ ነኝ። ዛሬ ምሽት፣ የነብያችንን ግብዣ ስከተል የተማርኳቸውን ሁለት ነገሮች አካፍላለሁ። ጥናቴ የመራበት ሰላም ሰጪ መንገድ ጌታ መሐሪ እንደሆነ እና የሰማይ አባታችን የደንነት እቅድ በእውነት የምሕረት እቅድ እንደሆነ አስታውሶኛል።

በቤተመቅደስ ውስጥ የሚያገለግሉ አዲስ የተጠሩ ሚስዮናውያን

እንደምታውቁት፣ “አዲስ የተጠሩ ሚስዮናውያን የቤተ መቅደስ ቡራኬን በተቻለ ፍጥነት እንዲቀበሉ እና ሁኔታዎች በሚፈቅዱት መጠን በቤተመቅደስ እንዲገኙ ይበረታታሉ።” አንዴ ቡራኬ ከተቀበሉ በኋላ “የሚስዮናዊነት አገልግሎት ከመጀመራቸው በፊት የቤተመቅደስ … ሰራተኞች ሆነው ሊያገለግሉ ይችላሉ።”

ወደሚስዮን ማሰልጠኛ ቦታ (MTC) ከመግባታቸው በፊት በቤተመቅደስ ውስጥ ያላቸው ጊዜ የለአዲስ ሚስዮናውያን አስደናቂ በረከት ሊሆን ይችላል፣ ምክንያቱም እነዚያን ቃል ኪዳኖች ለአለም ከማካፈላቸው በፊት ስለ ቤተመቅደስ ቃል ኪዳኖች የበለጠ ይማራሉና።

ነገር ግን ክፍል 109ን በማጥናቴ፣ በቤተመቅደስ ውስጥ፣ እግዚአብሔር አዳዲስ ሚስዮናውያንን—በእርግጥም ሁላችንንም—በተጨማሪ በተቀደሰ መንገድ ኃይል እንደሚሰጥ ተምሬያለሁ። በራዕይ በተሰጠው የምረቃ ጸሎት፣ ነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ “… ስለ ስምህ ምስክርነት ለመስጠት አገልጋዮችህ ከቤትህ በሚወጡበት ጊዜ፣” “የሰው ልጆች ሁሉ” “የምድር ታላላቆችም” ሆኑ “ድሆች፣ ችግረኞች፣ እና [የተጠቁት]” “ልባቸው እንዲራራ” በማለት ጸለየ። “አገልጋዮችህ ስለስምህ ለመመስከር ከቤትህ የሚወጡትን ልባቸው ያሰላስል ዘንድ፣ ጥላቻቸውም በእውነት ፊት ይከሰም ዘንድ፣ እና ህዝብህም በሁሉም አስተያየት ሞገስን ያገኙ ዘንድ፤ እኛ ባሪያዎችህ ድምፅህን እንደ ሰማን አንተም እንደላከን የምድር ዳርቻዎች ሁሉ ያውቁ ዘንድ” በማለት ጸለየ።

ይህ አዲስ ለተጠራ ሚስዮናዊ— “ህዝብህም በሁሉም አስተያየት ሞገስን ያገኙ ዘንድ” ጥላቻን” “በእውነት ፊት ይከሰም ዘንድ”፣የሚያደርግ ቃል ኪዳን ነው። ያለጥርጥር እያንዳንዳችን እነዚህ ተመሳሳይ በረከቶች ያስፈልጉናል። ከጎረቤቶች እና ከስራ ባልደረቦች ጋር በምንገናኝበት ጊዜ ልቦች መሰላሰላቸው ምን አይነት በረከቶች ይሆናሉ። የመመረቂያው ጸሎት በቤተመቅደስ ውስጥ ያለን ጊዜ እንዴት የሌሎችን ልብ እንደሚያራራ አይገልጽም፣ ነገር ግን በጌታ ቤት ውስጥ ያለው ጊዜ ኢየሱስ በክርስቶስ እና በምህረቱ እኛን በማማከል የራሳችንን ልብ እንደሚያራራ እርግጠኛ ነኝ።

ጌታ ለጆሴፍ ስሚዝ የምሕረት ልመና መልስ ሰጠ

የከርትላንድን የምረቃ ጸሎት ሳጠና፣ ጆሴፍ ለቤተክርስቲያኗ አባላት፣ ለቤተክርስቲያኗ ጠላቶች፣ ለአገሪቱ መሪዎች፣ ለምድር ህዝቦች ምህረትን ደጋግሞ መለመኑ አስገረመኝ። በግል፣ ጌታን እንዲያስታውሱት እና ለሚወዳት ኤማ እና ለልጆቻቸው እንዲራራላቸው ለምኗል።

ከአንድ ሳምንት በኋላ፣ በሚያዚያ 3፣ 1836 (እ.አ.አ)፣ በፋሲካ፣ በከርትላንድ ቤተመቅደስ፣ አዳኙ ለእሱ እና ለኦሊቨር ካውደሪ ሲገለጥ እና በትምህርተ እና ቃል ኪዳኖች ክፍል 110 ላይ እንደተመዘገበው፣ “እነሆ፣ ይህን ቤት ተቀብዬዋለሁ፣ እና ስሜም በዚህ ይሆናል፤ እና በምህረትም ራሴን ለህዝቤ አሳያለሁና” ሲል ጆሴፍ ምን ተሰምቶት ይሆን? ይህ የምሕረት ቃል ኪዳን ለጆሴፍ የተለየ ትርጉም ሳይኖረው አልቀረም። ፕሬዚዳንት ኔልሰን ባለፈው ሚያዚያ እንዳስተማሩት፣ ይህ ቃል ኪዳን እንዲሁ “ዛሬ ተመርቀው ለሚከፈቱ ቤተመቅደሶችም ሁሉ ይሠራል።”

በጌታ ቤት ምህረትን ማግኘት

እያንዳንዳችን በጌታ ቤት ውስጥ ምሕረት የምናገኝባቸው ብዙ መንገዶች አሉ። ጌታ ለመጀመሪያ ጊዜ እስራኤልን ድንኳን እንዲሠሩ እና “የምሕረት መቀመጫውን” በመካከሉ እንዲያስቀምጡ ካዘዘ ጊዜ ጀምሮ አሁንም ይህ እውነት ነው። በቤተመቅደስ ውስጥ በገባናቸው ቃል ኪዳኖች ውስጥ ምሕረትን እናገኛለን። ከጥምቀት ቃል ኪዳኑ በተጨማሪ እነዚያ ቃል ኪዳኖች ከአብ እና ከወልድ ጋር በማስተሣሰር ፕሬዚዳንት ኔልሰን በዕብራይስጥ “ሄሴድ የተባለ ልዩ ዓይነት ፍቅር እና ምህረት” እንደሆነ ያስተማሩትን በላቀ ደረጃ እንድናገኝ ያደርጉናል።

ለዘለአለም ከቤተሰቦቻችን ጋር ለመታተም ባለን እድል ምህረትን እናገኛለን። በቤተመቅደስ ውስጥ፣ እንዲሁም እያንዳንዱ የደሕንነት እቅድ ክፍል—ፍጥረት፣ ውድቀት፣ የአዳኙ የኃጢያት ክፍያ መስዋዕትነት እና እንደገና ወደ የሰማይ አባታችን መገኘት የመግባት ብቃታችን የምሕረት መገለጫ እንደሆነ ይበልጥ በግልጽ እንረዳለን። በትክክል “የምሕረት ዕቅድ” በመሆኑ ምክንያት የደህንነት እቅድ የደስታ እቅድ ነው ሊባል ይችላል።

ይቅርታን መፈለግ ለመንፈስ ቅዱስ በር ይከፍታል።

ክፍል 110 ጌታ በቤተመቅደሶቹ እራሱን በምሕረት እንደሚገልጥ ለሰጠው ውብ ቃል ኪዳን አመስጋኝ ነኝ። እኛም ልክ እንደ ጆሴፍ ምህረትን በምንለምንበት ጊዜ ጌታ ራሱን እንዴት በምሕረት እንደሚገልጥ ስለሚገልጸው ነገር አመስጋኝ ነኝ።

በክፍል 109 ላይ የሠፈረው የጆሴፍ ስሚዝ የምህረት ልመና፣ ልመናዎቹ ራዕይን ሲያነሳሱ የመጀመሪያ ጊዜ እንዳልነበረ ያሣያል። በተቀደሠ ጫካ ውስጥ፣ ወጣቱ ጆሴፍ የጸለየው የትኛው ቤተክርስቲያን እውነት እንደሆነ ለማወቅ ብቻ አልነበረም ነገር ግን “የምሄድበት ሌላ ማንም አልነበረውምና ወደ ጌታ ምሕረትን ለማግኘት” እንዳለቀሰ ተናግሯል።” በሆነ መንገድ ጌታ ብቻ የሚሰጠው ምህረት እንደሚያስፈልገው መገንዘቡ የሰማይ መስኮት እንዲከፈት ረድቶታል። ከሶስት አመታት በኋላ፣ ጆሴፍ “ሁሉን ወ[ደ]ሚገዛ እግዚአብሔር ለኃጢአቶ[ቹ] እና ለጥፋቶ[ቹ] ይቅርታ” ጠየቅኩበት ካለበት ጸሎት በኋላ መልአኩ ሞሮኒ ተገለጠ።

የምሕረት ልመናን ተከትሎ የሚመጣው ይህ የመገለጥ ንድፍ በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የታወቀ ነው። ሄኖስ የጌታን ድምፅ የሰማው ለይቅርታ ከጸለየ በኋላ ነበር። የንጉሥ ላሞኒ አባት መለወጥ “አንተን ለማወቅ ኃጢያቴን በሙሉ እተዋለሁ” በሚል ጸሎቱ ይጀምራል። በእነዚህ አይነት ተመሳሳይ አስደናቂ ልምዶች ላንባረክ እንችላለን፣ ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ለጸሎት መልስ እንዲሰማቸው ለሚቸገሩ፣ የጌታን ምሕረት መፈለግ የመንፈስ ቅዱስን ምስክርነት እንዲሰማን ከምናደርግባቸው በጣም ኃይለኛ ከሆኑ መንገዶች መካከል አንዱ ነው።

የእግዚአብሔርን ምሕረት ማሰላሰል ለመፅሐፈ ሞርሞን ምስክርነት በር ይከፍታል።

ሞሮኒ 10፥3–5 ላይ ተመሳሳይ ውብ የሆነ መርህ እንማራለን። ከልብ በሆነ ጸሎት፣ መፅሐፈ ሞርሞን እውነት መሆን አለመሆኑን ማወቅ እንደምንችል ለማስተማር ብዙ ጊዜ እነዚህን ጥቅሶች እናሳጥራቸዋለን። ነገር ግን እንዲህ ማሳጠር ለምሕረት ጠቃሚ ትኩረት እንዳይሰጥ ሊያደርግ ይችላል። ሞሮኒ ማሳሰቢያውን እንዴት እንደጀመረ አድምጡ፥- “እነዚህን ነገሮች በምታነቡበት ጊዜ፣…ከአዳም መፈጠር ጀምሮ እነዚህን ነገሮች እስከምትቀበሉበት ጊዜ ድረስ ጌታ ለሰው ልጆች ምን ያህል መሃሪ እንደነበረ እንድታስታውሱ እመክራችኋለሁ እናም በልባችሁ አስቡበት።”

ሞሮኒ እነዚህን ነገሮች ሊዘጋቸው የነበሩትን መዝገቦች እንድናነብ ብቻ ሳይሆን መፅሐፈ ሞርሞን “ጌታ ለሰው ልጆች ምን ያህል መሐሪ እንደነበረ” በልባችን እንድናሰላስል ያሳስበናል። “እነዚህ ነገሮች ሃሰት እንደሆኑ የዘላለም አባት እግዚአብሔርን በክርስቶስ ስም እንድንጠይቅ” የሚያዘጋጀን በጌታ ምሕረት ላይ ማሰላሰላችን ነው።

በመፅሐፈ ሞርሞን ላይ ስናሰላስል፣ እንዲህ እንጠይቅ ይሆናል፥ አልማ እንዳስተማረው፣ የእግዚአብሔር የምሕረት እቅድ በዚህ ምድር ላይ የኖረ ሰው ሁሉ እንደሚነሳ፣ በራሳቸው ላይ ያለው ፀጉር እንደማይጠፋ እና ወደ ፍፁም ሰውነታቸው እንደሚመለሱ የሚያረጋግጥ እውነት ነው?አሙሌክ የአዳኙ ምሕረት በእውነት እኛ መክፈል ያለብንን እና “በደህንነት እቅፍ ውስጥ እንድንከበብ የሚያስችለውን የፍትህ ጥያቄ ሁሉ ማርካት ይችላል” ያለው ትክክል ነው?

እውነት አልማ እንደመሰከረው ክርስቶስ ለኃጢአታችን ብቻ ሳይሆን [“ለህመማችን እና በሽታችን]” የተሰቃየው ህዝቡን በድካሙ እንዴት እንደሚረዳ ያውቅ ዘንድ ነው? ንጉሥ ቢንያም እንዳስተማረው፣ እንደ ነፃ ስጦታ፣ “… ለኃጢአተኞች፣ እነርሱን በተመለከተ ያለውን የእግዚአብሔር ፈቃድ ሳያውቁ ለሞቱት፣ ወይም ባለማወቅ ኃጢያትን ለፈፀሙት”31 በእውነት መሃሪ ነው?

ሌሂ “ሰዎች እንዲኖሩ፣ አዳም ወደቀ፤ እና ሰዎች የሚኖሩትም ደስታም እንዲኖራቸው ዘንድ ነው” ያለው እውነት ነው? አቢናዲ ኢሳይያስን ጠቅሶ እንደመሰከረው፣ ኢየሱስ ክርስቶስ “ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፣ ስለ በደላችንም ደቀቀ፣ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፣ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን” የሚለው በእርግጥ እውነት ነው?

በጥቅሉ፣ በመፅሐፈ ሞርሞን እንደተገለጸው የአብ እቅድ በእርግጥ የምህረት ነው? እንደዚያ እንደሆነ እና በመፅሐፈ ሞርሞን ውስጥ ያሉት ሰላም እና ተስፋ ሰጪ የምሕረት ትምህርቶች እውነት እንደሆኑ እመሰክራለሁ።

አሁንም፣ የሰማይ አባት “በመንፈስ ቅዱስ ኃይል እውነቱን ይገልፅላችኋል” የሚለውን የሞሮኒን ተስፋ ምንም እንኳን እናንተ በታማኝነት ብታነቡም እና ብትጸልዩም ለመረዳት አንዳንዶቻችሁ እንደምትቸገሩ እገምታለሁ። ይህን ትግል የማውቀው ከብዙ አመታት በፊት የራሴ የመጀመሪያዎቹ ሁለት የመፅሐፈ ሞርሞን ክፍሎች ለጸሎቶቼ ፈጣን እና ግልጽ መልስ ባልሰጡበት ጊዜ ስለተሰማኝ ነው።

እየታገላችሁ ከሆነ፣ መፅሐፈ ሞርሞን “ጌታ ምን ያህል መሐሪ እንደሆነ” በሚያስተምርባቸው ብዙ መንገዶች ላይ እንድታሰላስሉ የሞሮኒ ምክር እንድትከተሉ እጋብዛችኋለሁ። ካለኝ ልምድ በመነሳት፣ ይህን ስታደርጉ የመንፈስ ቅዱስ ሰላም ልባችሁ ውስጥ ይገባና መፅሐፈ ሞርሞን እና የሚያስተምረው የምሕረት እቅድ እውነት መሆኑን ማወቅ፣ ማመን እንዲሁም ሊሰማችሁ እንደሚችል ተስፋ አደርጋለሁ።

ለአብ ታላቅ የምሕረት እቅድ እና አዳኙም በፈቃደኝነት ስለፈጸመው ምስጋናዬን እገልጻለሁ። እርሱን ከፈለግን በቅዱስ መቅደሱ እና በሁሉም የሕይወታችን ክፍል በምሕረቱ ራሱን እንደሚገለጥ አውቃለሁ። በኢየሱስ ክርስቶስ ስም፣ አሜን።

ማስታወሻዎች

  1. ራስል ኤም. ኔልሰን፣ “Rejoice in the Gift of Priesthood Keys [በክህነት ቁልፎች ስጦታ ደስ ይበላችሁ]፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2024 (እ.አ.አ) ተመልከቱ።

  2. ራስል ኤም. ኔልሰን፣ “Rejoice in the Gift of Priesthood Keys [በክህነት ቁልፎች ስጦታ ደስ ይበላችሁ]፣” 121።

  3. አጠቃላይ መመሪያ መጽሃፍ፦ በኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ውስጥ ማገልገል፣ 24.5.1፣ የወንጌል ቤተመጻህፍት ተመልከቱ።

  4. ልክ እንደ ሁሉም የቤተመቅደስ በረከቶች፣ እግዚአብሔር የሚሰጠን በቤተመቅደስ ውስጥ የምንገባቸውን ቃል ኪዳኖች በመጠበቃችን ላይ የተመሰረተ ነው። የራስል ኤም.ኔልሰንን፣ “አለምን ማሸነፍ እና እረፍትን ማግኘት፣” ሊያሆና፣ ህዳር 2022 (እ.አ.አ)፣ 96፦ “በቤተመቅደስ ውስጥ ቃል ኪዳን የሚገባ—እና ቃል ኪዳኑን የሚያከብር—እያንዳንዱ ሰው የኢየሱስ ክርስቶስን ሀይል የማግኘት ተጨማሪ ችሎታ አለው።”

    እንደ ሌላ ምሳሌ፣ የቤተ መቅደሱን ልብስ ስለመለበሱ የቀዳማዊ ፕሬዚዳንቱን መግለጫ ተመልከቱ፥-”በቤተመቅደስ ቡራኬ የመጀመሪያ ክፍል ውስጥ በሚሠጠው መመሪያ መሰረት የቤተመቅደስ ልብስን የመልበስ እድልን ጨምሮ፣ ቃል ኪዳኖቻችሁን ስታከብሩ፣ የአዳኙን ምህረት፣ ጥበቃ፣ ጥንካሬና ሀይል በተሻለ ሁኔታ ታገኛላችሁ።(አጠቃላይ መመሪያ መጽሃፍ26.3.3.2፣ የወንጌል ቤተ መጻሕፍት)።

  5. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 109፥55null57

  6. ራስል ኤም. ኔልሰን፣ “ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ይመጣል፣” ሊያሆና፣ ህዳር 2024 (እ.አ.አ)፣ 121–22፦ ለእናንተ የምገባው ቃል ይህ ነው፦ ኢየሱስ ክርስቶስን በቅንነት የሚፈልጉ ሁሉ በቤተመቅደስ ያገኙታል። ምሕረቱ ይሰማችኋል።”

  7. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 109፥34: “ያህዌህ ሆይ፣ ምህረትህ በህዝብህ ላይ ምህረት ትሁን፣ እና ሁሉም ሰዎች ኃጢአትን ስለሚሰሩም፣ የህዝብህን መተላለፍ ይቅር በል፣ እና ለዘለአለምም ይደምሰስ።”

  8. ትምህርት እና ቃል ኪዳን 109፥50 ተመልከቱ።

  9. ትምህርት እና ቃል ኪዳን 109፥54 ተመልከቱ። እንዲሁም ጆሴፍ ጌታን እንዲህ ጠይቋል፥ “ምህረት በያዕቆብ ልጆች ላይ ትሆን ዘንድ፣ ከዚህ ሰአት ጀምሮ ኢየሩሳሌምን ቤዛነት ትጀምር ዘንድ እንጠይቅሀለን፤ እና የባርነትም ቀንበር ከዳዊት ቤት መሰበር እንዲጀምር፣ እና የይሁዳ ልጆችም ለአባታቸው አብርሐም በሰጠኸው ምድር መመለስ እንዲጀምሩ እንጠይቅሀለን”(ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 109፥62–64)።

  10. ትምህርት እና ቃል ኪዳን 109፥68 ተመልከቱ።

  11. ትምህርት እና ቃል ኪዳን 109፥69 ተመልከቱ። የኦክስፎርድ ኢንግሊዘኛ መዝገበቃላት ምሕረትን “ኃይል ለሌለው ሰው የሚደረግ ይቅርታና ርኅራኄ” ሲል ይገልጻል። ምህረት ልክ እንደ ጸጋ የእግዚአብሔር ፍቅር እና ደግነት መግለጫ ነው—የእርሱ ሃሴድምህረት የሚገባንን ቅጣት በመከልከል ላይ ያተኮረ ሲሆን ጸጋ የሚያመለክተው እግዚአብሔር የማይገባንን በረከቶች ሳናስብ ሲሰጠን ነው።

  12. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 110፥7

  13. ለግል የሆነውን ምሕረት መገለጫ፣ ጆሴፍ እና ኦሊቨር፣ “እነሆ፣ ኃጢአታችሁ ተሰርየዋል፤ በፊቴም ንጹህ ናችሁ፤ ስለዚህም፣ ራሳችሁን አቅኑ እናም ተደሰቱ” (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 110፥5) ተብለዋል።

  14. ራስል ኤም. ኔልሰን፣ “Rejoice in the Gift of Priesthood Keys [በክህነት ቁልፎች ስጦታ ደስ ይበላችሁ]፣” 119። ፕሬዚዳንት ኔልሰን “የጌታ ቃል ኪዳን በግለሰብ ደረጃ ለእናንተ ምን ትርጉም እንዳለው እንድታሰላስሉ እጋብዛችኋለሁ” ብለዋል።

  15. የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት ላይ “ድንኳን” ተመልከቱ፦ “ቅድስተ ቅዱሳን የያዘው አንድ ዕቃ ብቻ ነው፥ የቃል ኪዳኑ ታቦት። … በታቦቱ ላይ እንደ ክዳን የሚያገለግለው የስርየት መክደኛው ነበር። በአይሁድ ሕግ የሚታወቀው ከፍተኛው ሥርየት የተፈጸምበት መሠዊያ ሆኖ ከታቦቱ በታች በመሆን ያገለግል ነበር። የበስርየት ቀን በላዩ የኃጢአት መሥዋዕት ደም ይረጫል (ዘሌ. 16፥14-15)። የስርየት መክደኛው የእግዚአብሔር ክብር የሚገለጥበት ቦታ ነበር (ዘጸ. 25፥22)።”

  16. ራስል ኤም. ኔልሰን፣ “ዘለአለማዊ ቃል ኪዳን፣” ሊያሆና፣ ጥቅምት 2022 (እ.አ.አ)። ፕሬዚዳንት ኔልሰን እንዳመለከቱት፣ ሄሴድ ምንም ትክክለኛ የእንግሊዝኛ አቻ የለውም፣ ነገር ግን በብሉይ ኪዳን ውስጥ በጣም የተለመደው ትርጉሙ ምሕረት ነው። በብሉይ ኪዳን ኪንግ ጀምስ ትርጉም ላይ ሄሴድ የሚለው ቃል ከተገለጸበት 248 ጊዜ ውስጥ ምሕረት 149 ጊዜ፣ ደግነት 40 ጊዜ፣ እና አፍቃሪ ደግነት 30 ጊዜ ተጠቅሷል።

  17. General Handbook [አጠቃላይ መመሪያ መፅሐፍ] 27.2 ተመልከቱ። ሐዋርያው ዮሀንስ በአዳኙ ካልሆነ በቀር ማናችንም ብንሆም ወደ አብ መምጣት እንደምንችል ያስተምረናል (ዮሐንስ 14፥6 ይመልከቱ)። በትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ውስጥ፣ አዳኝ ለእኛ ምህረት ስለጠየቀበት ይህንን ውብ መግለጫ ይሰጣል፦

    “ከአብ ፊት አማላጅ የሆነውን፣ ፊቱም ስለእናንተ እንዲህ በማለት የሚማጸንላችሁን ስሙ--

    “አባት ሆይ ሀጥያት ያልሰራውን በእርሱም የተደሰትከውን ስቃይና ሞት ተመልከት፤ የፈሰሰውን የልጅህን ደም ተመልከት፣ ስምህ ይከበር ዘንድ አንተ የሰጠኸውን የልጅህን ደም ተመልከት፤

    “ስለዚህ፣ አባት ሆይ፣ በስምህየሚያምኑትን ወደ እኔም መጥተው ዘለአለማዊ ህይወት ይኖራቸው ዘንድ እነዚህን ወንድሞቼን አድናቸው” ት. እና ቃ. 45፥3–5

  18. ፕሬዚዳንት ጄፍሪ አር. ሆላንድ በአንድ ወቅት የተናገሩትን የሚከተለውን እወዳለሁ፥- “በእርግጥ እግዚአብሔር አምላክ በመሆኑ በጣም ከሚደሰትበት ነገር መካከል አንዱ መሐሪ፣ በተለይም ይህን ለማይጠብቁት እና ብዙ ጊዜ እንደማይገባቸው ሆኖ ለሚሰማቸው መሆኑ ነው፣ ነው” (“The Labourers in the Vineyard፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2012፣ 33)። ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 128፥19 ይመልከቱ፥ “አሁን፣ በተቀበልነው ወንጌል ውስጥ ምን እንሰማለን? የደስታ ድምፅ! የምህረት ድምፅ ከሰማይ፤ እና ከምድር ውስጥም የእውነትን ድምፅ፤ የምስራች ዜና ለሙታን፤ ከህያውና ከሙታን የደስታ ድምፅ፤ የታላቅ ደስታን የምስራች ነው።

  19. አልማ 42፥15። ምህረት ሁልጊዜም የመዳን እቅድ ማዕከል ነው። ሦስት የቅዱሳት መጻሕፍት ምንባቦች ምሳሌያዊ ናቸው። ኔፊ የመፅሐፈ ሞርሞንን የመጀመሪያ ምዕራፍ እንዲህ ሲል ይደመድማል፣ “ነገር ግን እነሆ እኔ ኔፊ የጌታ ምህረትንና ርህራሄ በእምነተታቸው ምክንያት በተመረጡት ላይ ሁሉ መሆኑንና እንዲሁምሀይይል እና እራሳቸውን ለማዳን የሚያስችላቸው መሆኑን አሳያችኋለሁ።” (1 ኔፊ 1፥20)

    ዘጸአት 34፥6 ላይ ጌታ ለሙሴ ስሙን “መሐሪ፥ ሞገስ ያለው፥ ታጋሽም፥ ባለ ብዙ ቸርነትና እውነት” በማለት ይናገራል። አንዳንዶች ይህ ጥቅስ ከሌሎቹ የብሉይ ኪዳን ጥቅሶች በበለጠ በብሉይ ኪዳን ነቢያት ሊጠቀስ እንደሚችል ይናገራሉ (see, for example, Bible Project, “The Most Quoted Verse in the Bible,” bibleproject.com/podcast/most-quoted-verse-bible/)።

    በአዲስ ኪዳን፣ በሉቃስ መጽሐፍ ውስጥ ዘካርያስ በእርጅናዋ ኤልሳቤጥ ወንድ ልጅ እንደምትወልድ የመልአኩን ተስፋ በተጠራጠረ ጊዜ “ዲዳ ትሆናለህ መናገርም አትችልም” እንደተባለ አስታውሱ (ሉቃስ 1፥20)። የዘካርያስ አንደበት በመጨረሻ በተፈታ ጊዜ፣ “በመንፈስ ቅዱስ ሞላበትና”፣ የመሲሑ ጊዜ በመጨረሻ እንደደረሰ በመጀመሪያ በአደባባይ ጌታ ለአባቶቻችን ፣ ምሕረት አደረገ፤ ለአባታችን ለአብርሃምም የማለውን መሐላውን ቅዱሱን ኪዳን አሰበ” ሲል “ትንቢት” ተናገረ” (ሉቃስ 1፥67፣ 72–73 አጽናኦት ተጨምሮበታል)።

  20. Gospel Topics Essays, “First Vision Accounts,” Gospel Library; see especially the 1832 account.

  21. የጆሴፍ ስሚዝ—ታሪክ 1፥29 ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 20፥5–6 በእነዚህ ራዕዮች ውስጥ ንስሀ መግባት ምን ሚና እንዳለው ሌላ መግለጫ ይሰጣል። ጆሴፍ “ማንም ሰው በማናቸውም ታላቅ ወይም አስከፊ ኃጢያት ጥፋተኛ ነህ ብሎ ሊያስብብኝ አይገባም” ብሏል፣ ነገር ግን እሱ “በድክመቶቹ እና ጉድለቶች የተወገዘ ሆኖ ተሰምቶት ስለነበር ይቅርታ አስፈልጎት ነበር (ጆሴፍ ስሚዝ—ታሪክ 1፥28፣ 29)።

  22. (ኢኖስ 1፥1-8 ይመልከቱ።)

  23. አልማ 22፥18። አልማ “የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ሆይ ምህረትህን በእኔ ላይ አድርግ”(አልማ 36፥17–20 በማለት የጸለየው ጸሎት በብርሃን ወደመሞላት እና ከህመም እፎይታ መርቷል። ፕሬዚዳንት ጄፍሪ አር. ሆላንድ በአንድ ወቅት ስለ አልማ ልመና እንዲህ ብለዋል፥- “እንዲህ አይነት ጸሎት አጭር ቢሆንም በወደቀ አለም ውስጥ ሊደረግ የሚችል በጣም አስፈላጊ ነው። ሌላ ምንም አይነት ጸሎቶች ብናቀርብም፣ ምንም አይነት ሌላ ፍላጎት ቢኖረን ሁላችንም ወደዚያ ልመና እንመለስ፥- “ኢየሱስ ሆይ ምህረትህን በእኔ ላይ አድርግ” (Our Day Star Risingሊያሆና Exploring the New Testament with Jeffrey R. Holland [2022]፣ 170–71)

  24. ሽማግሌ ካይል ኤስ ማኬይ በሚያምር ሁኔታ እንዲህ አስተምረዋል፣ “የጆሴፍ የዘወትር ንስሃ ህይወት ‘[ምህረትን እንዳገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በድፍረት እንድመጣ” አስችሎኛል” (“The Man Who Communed with Jehovah፣” ሊያሆና፣ Nov. 2024፣ 61)

  25. ሞሮኒ 10፥3

  26. “ነገር ግን እነሆ እኔ ኔፊ የጌታ ምህረትንና ርህራሄ በእምነተታቸው ምክንያት በተመረጡት ላይ ሁሉ መሆኑንና እንዲሁምሀይይል እና እራሳቸውን ለማዳን የሚያስችላቸው መሆኑን አሳያችኋለሁ።” (1 ኔፊ 1፥20)

  27. ሞሮኒ 10፥4

  28. ሞሮኒ 9፥13 ይመልከቱ።

  29. አልማ 40፥23፦ “ነፍስ ወደ ስጋ፣ ስጋም ወደ ነፍስ በዳግም ይመለሳል፤ አዎን፣ እናም ማንኛውም እጅና እግር እንዲሁም መገጣጠሚያ ወደ ቀድሞ ቦታው ይመለሳል፤ አዎን፣ የራስ ፀጉርም ቢሆን አይጠፋም፤ ነገር ግን ሁሉም ነገር ወደ ተገቢው እናም ትክክለኛ አቋሙ ይመለሳል።”

  30. አልማ 34፧16። ጌታ ምን ያህል መሐሪ እንደሆነ ስናስብ፣ የሰማይ አባታችን የፍቅር ምሕረት ብቻ ፍትሕን እንደሚያሸንፍ በማሰብ ምሕረትን ከፍትህ ለያይተን ለማየት ልንፈተን እንችላለን። ነገር ግን አልማ እንዳስተማረው፣ “የምህረት ዕቅድ የኃጢያት ክፍያው ካልተከፈለ በቀር ሊመጣ አይችልም፤ ስለዚህ፣ የምህረትን ዕቅድ ለመፈፀም፣ የፍትህን ፍላጎት ለማርካት፣ እግዚአብሔርም ደግሞ ፍፁም፣ እውነተኛ አምላክ፣ እናም መሃሪ አምላክ ይሆን ዘንድ፣ እግዚአብሔር እራሱ ለዓለም ኃጥያቶች የኃጢያት ክፍያ ይሆናልና” (አልማ 42፥15፤ አጽንዖት ተጨምሮበታል)።

    ሁሉም አዳኙ ለእኛ ያለው የምህረት ፍቅር ሊያድነን አልቻለም። ይልቁንም፣ እኛን የሚያዳነን የፍትህ ጥያቄዎችን የሚመልሰው የእርሱ እውነተኛ እና አሰቃቂ መከራ ነው። በእርግጥ ይህ የፍቅሩን አስፈላጊነት አይቀንስም። በእርግጥ፣ እርሱን ለመሰቃየት ፈቃደኛ እንዲሆን ያደረገው ለእኛ ያለው ፍቅር እና እኛን የሚወደንን የአብን ፈቃድ ለማድረግ ያለው ፍላጎት ነው (ዮሐንስ 3፥16ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 34፥3 ይመልከቱ)። ነገር ግን ፍቅር ብቻውን ሊሠራ አልቻለም።

    አንዳንድ ጊዜ፣ እንደ ተፈጥሯዊ ወንዶች እና ሴቶች ባህሪያችን ትእዛዛቱን ከመኖር የጎደ መሆኑን ረስተን—እኛ ባለንበት ሁኔታ እንዲሁ ይወደናል ብለን ፍትህ ፍላጎቱ እንዲረካ የሚጠይቅ መሆኑን ልንረሳ እንችላለን። ፍቅሩን በተሳሳተ መንገድ ከተረዳን እና የፍትህ ጥያቄዎችን እንደሚያስወግድ ካየነው፣የእርሱን የስርየት መስዋዕትነት ስጦታ እና ለፍትህ አስከፊ መስዋዕትነት የከፈለውን መከራ ዋጋ እንቀንሳለን። ለእኛ ያለው ፍቅር የኃጢያት ክፍያ መስዋዕቱን አላስፈላጊ እንዳልሆነ ከተረዳን ተስፋ የሚያስቆርጥ ነው። ሙሉ የፍትህ ጥያቄዎችን በትክክል መመልከታችን እና እኛን ወክሎ እነዚያን ትክክለኛ ጥያቄዎች ለመሸከም ስለወደደን አመስጋኞች መሆን ምንኛ የተሻለ ነው።

  31. አልማ 7፥11-12

  32. ሞዛያ 2፥41

  33. 2 ኔፊ 2፥25

  34. ሞዛያ 14፥5

  35. ሞሮኒ 10፥4

  36. ሞሮኒ 10፥3

  37. ፕሬዚዳንት ኤም ሩሰል ባላርድ “ስለምናውቀው እና ስለምናምነው እናስለሚሰማን” እንድንመሰክር አበረታቱን (“Remember What Matters Most፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2023 (እ.አ.አ)፣ 107፤ በዋናው ላይ አትኩሮት አለ)።

  38. ይህንን ሃሳብ በማቅረቤ፣ ለመፅሐፈ ሞርሞን ወይም ለወንጌል እውነትነት ምስክር የሚሆን ምትክ “ቀመር” ለማቅረብ አላስብም። ሽማግሌ ዴቪድ ኤ. ቤድናር እንዳስተማረው፣ ራዕይ “በጨለማ ክፍል ውስጥ እንደበራ ብርሃን” ሊመጣ ይችላል፣ ይህም ራዕይ “በፍጥነት፣ ሙሉ በሙሉ እና ሁሉም በአንድ ጊዜ” ነው። እንዲሁም እንደ “ፀሐይ ጀምበር የሚፈነጥቀው ብርሃን ቀስ በቀስ በመጨመር፣ … መስመር ላይ፣ ትእዛዝ ላይ ትእዛዝ (2 ኔፊ 28፥30) ሊሆን ይችላል።. … ከሰማይ አባት የሚመጡ እንደዚህ ያሉ ግንኙነቶች ቀስ በቀስ እና በእርጋታ ‘ በነፍሳችን ላይ እንደ ሰማይ ጠል ትንጠባጠባለች’ (ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 121፥45)። ይህ የመገለጥ ንድፍ ይበልጥ የተለመደ ነው” (“The Spirit of Revelation፣” ሊያሆና, May 2011, 88).