ለአዳኙ ያለኝ ፍቅር የእኔ “ምክንያት” ነው።
አዳኛችንን እወደዋለሁ። ይህም የማደርገውን የማደርግበት እውነተኛ እና ሀይለኛ ምክንያት ነው።
ውድ ነቢያችን ፕሬዚዳንት ራስል ኤም. ኔልሰን ያለማቋረጥ ግብዣ እንደሚያቀርቡልን አስተውላችኋል? ባለፉት ሁለት ጉባኤዎች የተላለፉተን መልዕክቶች እንድናጠናና እንድናሰላስል መጋበዛቸው አያስገርምም። በሚያዝያ 2024 (እ.አ.አ) ላይ፣ እንዲህ ብለዋል፣ “በሚቀጥሉት ወራት፣ የዚህን ጉባኤ መልዕክቶች ደጋግማችሁ እንደምታጠኑ ተስፋ አደርጋለሁ።” ከዚያም በጥቅምት 2024 (እ.አ.አ) ላይ እንዲህ አሉ፣ “መልዕክቶቻቸውን እንድታጠኑ በቅንነት አበረታታችኋለሁ። እነዚህን እንደ ሊትመስ ወረቀት፣ እውነት የሆነውን እና ያልሆነውን ለመለየት ለመጪዎቹ ስድስት ወራት ተጠቀሙባቸው።”
እነዚህ ግብዣዎች በሕይወታችን በሙሉ ከተቀበልናቸው ትንቢታዊ ግብዣዎች ጋር ሊደመሩ ይችላሉ፣ በተለይም በቅርብ ዓመታት ውስጥ የተቀበልናቸውን ጨምሮ። እነዚህ ግብዣዎች እኛ ስለተጋበዝን ወይም ስለተጠየቅን ብቻ ወደ ማድረግ ያለብን ዝርዝር ውስጥ ማከል ያለብን ሌላ ነገር ነው ብለን ሊሰማን ወይም እናስብ ይሆናል። ግን ከዚህ የበለጠ ምክንያት ሊኖረው ይችላልን?
በዚህና በተቀበልናቸው ግብዣዎች ሁሉ ላይ ሳሰላስል ከረጅም ጊዜ በፊት የተማርኩትንና የወሰንኩትን አንድ ነገር አስታወስኩ። እነዚህን ነገሮች ለማድረግ እየሞከርኩ ነው፣ ይህም ለእኔ አስፈላጊ ነው ምክንያቱም እሱን ስለምወደው፤ አዳኜን እወደዋለሁ። እኔ የማደርገውን የማደርግበት ትክክለኛ እና ዋነኛው ምክንያት ይህ ነው፣ ለወንድሞቼና ለእህቶቼ ያለኝ ፍቅር ከዚህም ጋር የተያያዘው ነው።
ወንድማችሁ እንደመሆኔ መጠን፣ የምናደርገውን ነገር ሁሉ ለአዳኙ ካለን ፍቅር ጋር ለማገናኘት ቃላቶቼን እንደ ልባዊ ግብዣ አድርጋችሁ እንደምትመለከቱት ተስፋ አደርጋለሁ።
ይህንን ማድረጋችን እንደ አዳኙ ደቀመዛሙርት ከምንሰራው ነገር ሁሉ በስተጀርባ ያለውን ትክክለኛ “ምክንያት” እንድንረዳ ይረዳናል። ይህ ከእግዚአብሔር ጋር ያለንን የቃል ኪዳን ግንኙነት እንድናጠናክር ይረዳናል፣ የእርሱን መለኮታዊ እና ዘለአለማዊ እውነቶች፣ መቼም የማይለወጡትን የእርሱን ዘለአለማዊ እና ፍጹም እውነቶች እንድንረዳ ይረዳናል። ልክ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና” እንደሚለው አይነት ዘለአለማዊ እውነት።
አንዳንድ ጊዜ በተከታታይ የምናደርጋቸው ነገሮች ወደ ወግነት ስለሚያደርሱ እነዚህ ወጎች ወይም እንቅስቃሴዎች በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ እምነት ለመገንባት የምናደርገውን ጥረት እንዲቆጣጠሩ መፍቀዳችን ትኩረት የሚስብ ነው። እነዚህን ነገሮች የምናደርገው ከአዳኛችን ጋር ባለን የቃል ኪዳን ግንኙነት ላይ የሚያሳድረውን ተጽዕኖ ሳናስብ ለብዙ ዓመታት ስላደረግናቸው ይመስላል።
በዓለማችን ውስጥ አብዛኛውን ጊዜ የምናተኩረው በምንሰራው ነገር ላይ እና ተግባሮችን እና ግቦችን በተከታታይ በማከናወን ላይ ነው። በመንፈሳዊው መስክ ለምን እንደምናደርገው በመረዳት ነገሮችን ከማድረግ ወይም ግቦችን ከማሳካት ባሻገር ለመሄድ ዕድሉ አለን። ከድርጊታችን በስተጀርባ ያለው ምክንያት ከመድኃኒታችን እና ከሰማያዊ አባታችን ጋር ካለን ፍቅር ጋር የተያያዘ መሆኑን በመረዳት እና በማገናኘት ከቻልን እነዚህን አጋጣሚዎች በመጠቀም ምንም እንኳን እንደ ቤተክርስቲያን እንቅስቃሴዎች ወይም ወጎች የመሳሰሉ ትክክለኛ ነገሮችን ማከናወን እና በተገቢው መንገድ ማከናወን ጥሩ ነገር መሆኑን እንገነዘባለን፣ ለምን እንደሆነ ካገናኘናቸው ምክንያቱን በመረዳት እንባረካለን። መልካም ነገሮችን ማድረግ ወይም በትክክል ማድረግ ብቻ ሳይሆን በትክክል ማድረግም ጭምር ነው።
ለምሳሌ ያህል፣ ጥቅሶችን ለማንበብ፣ ከልብ የመነጨ ጸሎት ለማቅረብ ወይም ለቤተሰባችሁ ወይም ከአጥቢያ አባላት አንድ ዝግጅትን ለማዘጋጀት ግብ ስታወጡ እውነተኛ ግባችሁ እነዚህን ነገሮች ማከናወን ብቻ ነውን? ወይስ እነዚህ እርምጃዎች እውነተኛውን ግብ ለማሳካት የሚያስችላችሁ መሣሪያዎች ናቸውን? ዓላማው፣ አንድን ሥራ ለብዙ ዓመታት ስናከናውን ስለመቆየት፣ ከዚያም ሥራውን አጠናቀናል የሚለውን ሣጥን ምልክት ስለማድረግ ብቻ ነው? ወይስ እነዚህ እንደገና ከአዳኙ ጋር ለመማር፣ ለመሰማትና ለመገናኘት የምንጠቀምባቸው መንገዶች ናቸው?
እባካችሁ እንቅስቃሴዎቻችሁን እና ወጎችን ስለማድረግ ወይም ግቦችን ስለማውጣት እና እነሱን ለማሳካት ጠንክሮ ስለመስራት ያለኝን ነጥብ በተሳሳተ መንገድ አትረዱ፤ በዚህ ውስጥ ምንም ስሕተት የለም። ይሁን እንጂ እነዚህን ነገሮች ለምን እንደምናደርግ እና እምነታችንን እንዴት እንደምንለማመድ ለመረዳት ዕድሉን እና በረከቱን ልባችሁን እና አዕምሮዎችሁን እንዲከፍት እጋብዛችኋለሁ።
በክርስቶስ ላይ ያተኮሩ ባህሎች ዋና ምሳሌ ፕሬዚዳንት ዳለን ኤች. ኦክስ በቀዳሚ አመራር ስም ለሁላችንም ያቀረቡት ፈተና ነው። ፕሬዚዳንት ኦክስ እንዲህ ብለዋል፣ ”ወደ አዲሱ ዓመት ስንገባ የኢየሱስ ክርስቶስን የኃጢአት ስርየት በዓል ለማክበር ራሳችንን እናዘጋጅ። ሌሎች ሰዎች የሚያምኑት ወይም የሚያደርጉት ነገር ምንም ይሁን ምን፣ የእርሱን ትምህርቶች በማጥናት እና በመላው ህብረተሰባችን በተለይም በቤተሰባችን ውስጥ የፋሲካ ባህልን ለማቋቋም በመርዳት የሕያው አዳኛችንን ትንሣኤ ማክበር አለብን።” እንደምታዩት ባህሉ እንዲኖረን የተደረገ ግብዣ ብቻ አይደለም። ይልቁንም እነዚህን ባህሎች ስለ አዳኙ የበለጠ ለመማር እና ትንሣኤውን እንደማስታወሻ መንገድ እንጠቀማለን።
ምክንያቱን ከአዳኙ ፍቅር ጋር ማገናኘት በቻልነው መጠን የሚያስፈልገንን ወይም የምንፈልገውን ነገር ማግኘት እንችላለን። ፕሬዚዳንት ኔልሰን እንዲህ ብለዋል፣ “ምንም አይነት ጥያቄዎች ወይም ችግርች ቢኖሯችሁ፣ መልሱ ሁልጊዜም በኢየሱስ ክርስቶስ ህይወት እና ትምህርት ውስጥ ይገኛል።” ከዚያም የሚከተለውን ግብዣ አቅርበዋል፦ “ስለኃጢያት ክፍያው፣ ፍቅሩ፣ ምህረቱ፣ አስተምሮቱ፣ እና በዳግም ስለተመለሰችው የፈውስ እና የእድገት ወንጌሉ የበለጠ ተማሩ።” ፊታችሁን ወደ እርሱ መልሱ! እርሱን ተከተሉ!”
ይህን በልባችሁና በአዕምሮአችሁ አስቡት፦ የፕሬዚዳንት ኔልሰን ግብዣ ተጨማሪ እውቀትን የምናከማችበትና ስራዎችን የምናጠናቅቅበት የማረጋገጫ ዝርዝር ለማዘጋጀት ይረዳናል ብላችሁ ታምናላችሁን? ወይስ የእነዚህን ዘለአለማዊ እውነቶችና መርሆዎች ገጽታዎች ለምን እንደሆነ እንድንረዳና የአዳኙን የቃል ኪዳን ፍቅር ከዕድሜ ልክ ደቀ መዝሙርነት ጉዞአችን ጋር እንድናገናኘው እየጋበዙን ናቸውን?
ለማስተላለፍ የሞከርኩትን መርህ በምሳሌ ላስረዳ። አንደኛው አማራጭ፣ ምናልባትም ጽንፈኛ የሚሆነው፣ ሁሉንም የጉባኤውን መልእክቶች ማንበብ እና አንዴ ከጨረስኩ በኋላ፣ ባነበብኩት ሌላ ምንም ነገር ሳላደርግ ይህን ግብዣ ከስራ ዝርዝርዬ ውስጥ መሰረዜ ሊሆን ይችላል። ይህ እጅግ አስከፊ ሁኔታ እንደሆነ እገነዘባለሁ፤ ነገር ግን ከእውነታው የራቀ አይደለም። ምናልባትም ብዙዎች በዚህና በተገቢው መካከል ባለንበት ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
ግብዣው፣ ከአጠቃላይ ጉባኤ የተላለፉ መልዕክቶችን ማጥናት እና ማሰላሰል እና እያንዳንዳችን ለማሻሻል ምን ማድረግ እንደምንችል ለመወሰን እና ለመረዳት እነሱን መጠቀም ነው።
ግብዣውን ስንቀበል፣ ከኋላው ያለውን “ለምን” የሚለውን ስንረዳ፣ ወደ አዳኙ ለመቅረብ ብዙ እድሎች ይኖሩናል። አዳኙን ስለምወድ በህይወት ያሉ ነቢያትን ቃል በማጥናት ስለ እርሱ የበለጠ መማር እንደምፈልግ መረዳት እንጀምራለን። ባልንጀራዬን ስለምወድ፣ ከምወዳቸው ሰዎች ጀምሮ የነቢያትን፣ የገላጮችንን እና የባለራዕዮችን ትምህርት ለሌሎች አካፍላለሁ።
በሁለቱም ምሳሌዎች ትክክለኛውን ነገር እያደረጋችሁ ነው። በአንደኛው፣ ግቡ የሰማይ አባት እና አዳኙ የሰጡንን መንገድ መጠቀም ይመስላል፣ ይህም በአጠቃላይ ጉባኤው ወቅት የሚጋሩ መልዕክቶች ናቸው። ሁለተኛው ደግሞ መሰረታዊ የሆኑትን ምክንያቶች ለመረዳት የሚያስችል ጥልቅ በረከትን ያጠቃልላል፣ ይህም ዘለአለማዊ እውነቶችን ለመረዳት የሚያስችል መንገድን ያቀርባል እንዲሁም የአዳኛችን የኢየሱስ ክርስቶስን ትምህርቶችና ሕይወት የሕይወታቸው ማዕከላዊ ነጥብ ለሚያደርጉ ሁሉ የተስፋ በረከቶችን ይሰጣል።
ውድ ወንድሞቼና እኅቶቼ፣ ተግባሮቻችንን ከአዳኙ ፍቅር ጋር ማገናኘት ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ እንደምትገነዘቡ ተስፋ አደርጋለሁ። በዓለም አቀፋዊነት በተሞላው ዓለም ውስጥ፣ ብዙ ድምፆች በእናንተ ላይ ተጽዕኖ ለማሳደር በመሞከር፣ ከተቻላቸውም፣ በዳግም የተመለሰው የኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል አንዳንድ መሰረታዊ እውነቶች አላስፈላጊ ናቸው ብላችሁ እንድታምኑ ሊመሯችሁ ይጥራሉ። እነዚህ ድምጾች የሚጀምሩት በእነዚህ የመጨረሻ ቀናት የዳግም መመለስ አስፈላጊነት እውነት የእግዚአብሔር መንግስት በምድር ላይ እንዲኖር አስፈላጊ መሆኑን ጨምሮ፣ ይህም በዳግም የተመለሰው የኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው።
ከአዳኙ ጋር የግል ግንኙነት ወይም መግባባት ብቻ በቂ እንደሆነ እና ሀይማኖት ወይም በዳግም የተመለሰችው ቤተክርስቲያን አላስፈላጊ ወይም ጠቃሚ እንዳልሆኑ የሚናገሩ ድምፆችን ልትስሙ ትችላላችሁ። እነዚህን አሳሳች አስተሳሰቦች በጥልቅ እንድታስቡበት ወይም ወይም ለማጤን ተጽዕኖ እንዳያሳድሩባችሁ እንድታደርጉ፣ እንዲሁም የሰማያዊ አባታችን እና ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ካላቸው ፍቅር በመነሳት እና ለእነሱ ያለንን ፍቅር እነሱን ለመከተል እንደ ምክንያት አድርገን በማገናኘት፣ አዳኙ ከጥንት ጊዜያት ጀምሮ እየነገረንና እያስተማረን ያለውን ለማስታወስ ፈጣን እንድትሆኑ እጋብዛችኋለሁ።
እግዚአብሔር አብ እና ልጁ መጥተው ከጆሴፍ ስሚዝ ጋር የኢየሱስ ክርስቶስን ቤተክርስቲያን መልሰው ለማቋቋም እና የዘመናት ፍጻሜ የሆነውን የእርሱን መንግሥት በምድር ላይ ለማቋቋም ተነጋግረዋል። ስለዚህ የኋላኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን የሰማይ አባታችን ወደ ቤት እንድንመለስ የሚያስችሉን ቃል ኪዳኖችን ለመድረስ ያቋቋመው መንገድ ነው። ስለዚህ ከሰማያዊው አባታችንና ከልጁ ጋር የግል ዝምድና ከመመስረት ያለፈ ነገር ያስፈልገናል፤ ከእነሱ ጋር ቃል ኪዳን የምንገባባቸው መሰረታዊ የክህነት ሥርዓቶች ያስፈልጉናል። ይህም ከእነሱ ጋር የቃል ኪዳን ግንኙነት እንዲኖረንና የቃል ኪዳናቸው ፍቅር እንዲኖረን ያስችለናል፤ ይህም ቃል ኪዳናቸውን በታማኝነት ለሚጠብቁ ሰዎች የተዘጋጀውን የላቀውን የክብር መንግሥት ማግኘት እንድንችል ያስችለናል።
የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን እውነተኛነትና መለኰታዊነት በሙሉ ነፍሴ እመሰክራለሁ። ይወዳችኋል። በሕይወታችሁ ውስጥ ምን እየተከናወነ እንዳለ ያውቃል። “ወደ እኔ ኑ፣ … እኔም አሳርፋችኋለሁ” በማለት እጁን ዘርግቶ ግብዣውን ያቀርባል።
አዳኙን እወደዋለሁ፤ ለእርሱ ያለኝ ፍቅር ደግሞ “ምክንያቴ ነው። በኢየሱስ ክርስቶስ ስም፣ አሜን።