አጠቃላይ ጉባኤ
በላያችን ላይ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም መውሰድ
የጥቅምት 2025 (እ.አ.አ) አጠቃላይ ጉባኤ


13:22

በላያችን ላይ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም መውሰድ

ለእኛ፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ባወቅን እና ባስታወስን ቁጥር እርሱን መምሰል እንሻለን።

በ2018 (እ.አ.አ)፣ በዩታ ዩኒቨርሲቲ፣ “የዶ/ር ራስል ኤም. ኔልሰን እና ዳንትዜል ደብሊው. ኔልሰን ፕሬዘደንታዊ ረስልኤም. ኔልሰን እና ዳንትዝልደብሊው. ኔልሰን በካርዲዮቶራክቲክ ቀዶ ጥገና ውስጥ የፕሬዚዳንት ሊቀመንበር” ካርዲዮ ማለት “የልብ” እና [ቶራክቲክ] ማለት “የደረት።” የፕሬዘዳንት ኔልሰንን አስፈላጊ ለሆነው የልብ ቀዶ ጥገና ሐኪምነታቸው እና ከቀድሞ ባለቤታቸው ዳንትዝል ላገኙትም ድጋፍ ክብርን ሰጥቷል። ይህ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተከፈለው ለወደፊትም እንዲቆይ ተብሎ በተዘጋጀ የገቢ እርዳታ ነው። ለዚህ አይነቱ ታዋቂ የፕሮፌሰርነት ማዕረግ የተመረጠ ግለሰብ የእውቅና፣ የደመወዝ ድጋፍ እንዲሁም የምርምር ገቢ እርዳታዎችን ይቀበላል።

ዶ/ር. ሰልዝማን ከፕሬዚዳንት ኔልሰን ጋር

የፕሮፌሰርነትን ማዕረግ ለመያዝ የተመርጠው የመጀመሪያው የቀዶ ጥገና ሐኪም የነበሩት ዶ/ር ክሬግ ኤች ሴልዝማን ሲሆኑ፣ የቤተክርስቲያናችን አባል ያልሆኑ ስልጡን የልብ ቀዶ ጥገና ሐኪም ነበሩ። ይህንን የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ለዶ/ር ሴልዝማን ለማበርከት ፕሬዚዳንት ኔልሰን እና ባለቤታቸው እህት ዌንዲ ደብሊው ኔልሰንን ጨምሮ ሌሎች ብዙ የክብር እንግዶች ተገኝተው ነበር። በስብሰባውም ወቅት፣ ፕሬዘደንት ኔልሰን በትህትና ስለ ፈር ቀዳጅ የቀዶ ጥገና ስራቸው ተናገሩ።

ከዚያም ዶ/ር ሴልዝማን ቀጥለውም ለዚህ ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መሾም ለእርሳቸው ምን ማለት እንደሆነ አካፈሉ። ከአራት ቀናት በፊት፣ በቀዶ ጥገና ህክምና ክፍል ውስጥ ለረጅም ቀን ቆይታ በኋላ አንድ ታካሚ ለቀዶ ጥገና መመለስ እንዳለበት ተገነዘቡ። ሌላ ምሽት በሆስፒታል ማሳለፍ እንዳለበት ሲያውቅ ድካም እና የሀዘን ስሜት ተሰማው።

ዶ/ር. ሴልዝማን ከእህት እና ከፕሬዘዳንት ኔልሰን ጋር

በዚህ ምሽት፣ ዶ/ር ሴልዝማን ከራሳቸው ጋር ሕይወትን የሚቀይር ንግግር አደረጉ። በጊዜውም፣ “አርብ ዕለት፣ በዶ/ር ኔልሰን ስም በተሰየመው የፕሮፌሰርነት ማዕረግ እሾማለሁ ብሎ አሰበ። ሁልጊዜም ስሜታቸውን በመቆጣጠር፣ ለሁሉም ሰው አክብሮት በመኖር እና ትዕግስተኛ በመሆን ይታወቃሉ። አሁን ስሜ ከእርሳቸው ጋር ስለሚያያዝ፣ እርሳቸውን ለመምሰል ጥረት ማድረግ አለብኝ።” ዶ/ር ሴልዝማን በዚያ ጊዜ ታዋቂ የቀዶ ጥገና ዶክተር ነበሩ። ነገር ግን ከዚያም የተሻለ ለመሆን ፈለጉ።

በባለፉት ጊዜያት፣ የቀዶ ጥገና ቡድናቸው የእርሱን ድካምን እና ብስጭት ያውቁ ነበር፣ ምክንያቱም እርሱ ይህን በጸባዩ እንዲሁም በንግግሩ ውስጥ በእንዲታይ ያደርግ ነበር። ነገር ግን በዚያ ምሽት በቀዶ ጥገና ክፍል ውስጥ፣ ዶ/ር ሴልዝማን በተለይ ቡድኑን ለመደገፍ እና ለመረዳት ከፍተኛ ጥረት አደረገ። ለውጥ እንዳመጣ ተሰማው እናም እንደ ዶ/ር ኔልሰን ለመሆን መሞከሩን ለመቀጠል ወሰነ።

ዶ/ር. ሰልዝማን የRMN አርማን አድርጎ

ከአምስት ዓመታት በኋላ፣ ፕሬዘደንት ኔልሰን በሙያ የሰለጠኑበትን ወረቀቶቻቸውን ለዩታ ዩኒቨርሲቲ ለገሱ። ፕሬዘዳንት ኔልሰንን ለማመስገን ከዩኒቨርሲቲው የተወከሉ ሰዎችም መጡ። በዚህ ዝግጅት ወቅት፣ ዶ/ር ሴልዝማን እንደገና ተናገረ። የፕሬዘዳንት ኔልሰን የስማቸው የመጀመሪያ መነሻን RMNን በመጥቀስ፣ “አሁን በዩታ ዩኒቨርሲቲ የልብ ቀዶ ጥገና ቡድን ክፍልን ሥነ-ምግባር ጠብቆ የሚያቆይ የ‘RMN’ ተጽዕኖ አለ” በማለት ተናገሩ።

በአስጨናቂ ሁኔታዎች ውስጥ፣ ዶ/ር ሴልዝማን እንዲህ ሲሉ ገጿል፣ “አሁን ሰልጣኞቻችን እንዲያደርጉ የምናስተምረውን—ትኩረት ማድረግ፣ ወደ ፊት መቀጠል፣ እና የምትችሉትን ሁሉ ማድረግ። ይህ ሥነ-ምግባር ሁል ጊዜም በውስጣችን ይኖራል። ለእያንዳንዱ ክፍል አባል እና ለእያንዳንዱ አዲስ ሰልጣኝ የላፔል አርማን እንሰጣለን። በአርማውም ግርጌ ‘RMN’ የሚሉት ፊደሎች ይገኛሉ። የ RMN ሥነ-ምግባር ለሥልጠናችን መሠረት ነው ለሁሉም እናስተምራለን።” ዶ/ር ሴልዝማን የቀድሞ አመለካከታቸውን እና ምኞታቸውን አሻሽለዋል ምክንያቱም ስማቸው አሁን ከፕሬዘዳንት ኔልሰን ስም ጋር የተቆራኘ በመሆኑ።

ከዶ/ር ሴልዝማን ጋር የተያያዙት እነዚህ ተከታታይ ክስተቶች “ስሜን ከኢየሱስ ክርስቶስ ስም ጋር ካገናኘሁ በኋላ እንዴት ነው የተለወጥኩት?” ብዬ እራሴን እንድጠይቅ አድርገውኛል። በውጤቱ የክርስቶስን ዓይነት ሥነ ምግባርን ተቀብያለሁን? ለመሻሻል እና እርሱንስ ለመምሰል በእውነት ሞክሪያለሁን?”

በዶ/ር ሴልዝማን ልምድ፣ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በራሳችን ላይ ከምንወስድበት ሂደት ጋር ቢያንስ አምስት ማመሳሰያዎችን ማየት እንችላለን። ምንም እንኳን ይህ ሂደት በጥምቀት ቢጀምርም፣ እኛ የበለጠ ንጹህ እና ቅዱስ እስክንሆን እና እርሱን እስክንመስል ድረስ ሙሉ በሙሉ ፍጹም አይደለም።

የመጀመሪያው ማመሳሰያ መታወቅ ነው። ዶ/ር ሴልዝማን ለኔልሰን ፕሮፌሰርነት ማዕረግ መሾማቸው ስማቸውን ከፕሬዘደንት ኔልሰን ያገናኘዋል እና ዶ/ር ሴልዝማን ከፕሬዘዳንት ኔልሰን ጋር መታወቅ ጀመሩ። የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በራሳችን ላይ ስንወስድ፣ ስማችንን ከእርሱ ጋር እናገናኛለን። ከእርሱ ጋር አብራን እንታወቃለን። በደስታም ክርስቲያን ተብለን እንጠራለን። አዳኝን አምነን ተቀብለናል እናም ያለ ፍርሃት እንደ እርሱ ለመቆጠር ቆመናል።

ከመታወቅ ጋር በቅርበት የተዛመደ ሌላ ማመሳሰያ—ትውስታ ነው። ዶ/ር ሴልዝማን ወደ ቢሮአቸው ሲገቡ፣ ለኔልሰን ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሲሾሙ ወደ ተቀበሉት ሜዳሊያ ዓይናቸው ተሳበ። ይህ ሜዳሊያ በየቀኑ የRMN ስነ ምግባርን ያስታውሳቸዋል። ለእኛ፣ በየሳምንቱ ቅዱስ ቁርባን መካፈላችን ኢየሱስ ክርስቶስን በሳምንቱ ውስጥ ሁሉ እንድናስታውስ ይረዳናል። ቅዱስ ቁርባንን ስንካፈል፣ እኛን ለመቤዠት የከፈለውን ዋጋ በማስታወስ እንካፈላለን። እርሱን ለማስታወስ፣ ታላቅነቱን ለማወቅ እና ቸርነቱን ለማድነቅ እንደ አዲስ ቃል ኪዳን እንገባለን። ከሥጋዊና ከመንፈሳዊ ሞት የዳንነው በእርሱ አማካኝነት እና በእርሱ በኩል ብቻ ጸጋን ማግኘት እንደቻልን ደጋግመን እናሳውቃለን ።

ማስታወስ ማለት የመፅሐፈ ሞርሞን ነቢይ የሆነው አልማ የሰጠውን ምክር እንከተላለን ማለት ነው። እኛ “[ስራችንን] ሁሉ ለጌታ ይሁን፣ እናም ወደ የትኛውም ሥፍራ [ብንሄድም] በጌታ ይሁን፤ … [እኛ]፣ [ሀሳባችንን] ሁሉ በጌታ የተመራ ይሁን፤ … [እናም እኛ] [የልባችንን] ዝንባሌ ለዘለዓለም በጌታ ላይ ይሁን። በሌሎች ጉዳዮች በተጠመድን ጊዜ እንኳን፣ ትኩረታችን ምንም ይሁን ምን የራሳችንን ስም እንደምናስታውስ ሁሉ፣ እርሱንም ደግሞ እናስታውሳለን።

አዳኝ ያደረገልንን ማስታወስ የሚያበለጽገው ሦስተኛው ማመሳሰያ—መምሰል ነው። ዶ/ር ሴልዝማን ፕሬዘዳንት ኔልሰንን እና የRMN ሥነ-ምግባርን መምሰል ጀመሩ። የፕሬዘደንት ኔልሰን ስነ-ምግባር የኢየሱስ ክርስቶስ የህይወት ዘመን ደቀ መዝሙርነት መገለጫ እንደሆነ አምናለሁ። ለእኛ፣ ኢየሱስ ክርስቶስን ባወቅን ቁጥር እና ባስታወስን ቁጥር እርሱን መምሰል እንሻለን። እንደ እርሱ ደቀ መዝሙርነታችን፣ እኛ በራሳችን ላይ ከማተኮር ይልቅ በእርሱ ላይ ስናተኩር ወደ ተሻለ ምልኩ እንለውጣለን። እርሱን ለመምሰል እንተጋለን እናም በእርሱ ባህሪያት መባረክ እንፈልለጋለን። ንጹህ የክርስቶስ ፍቅር በሆነው፣ በበጎ አድራጎት እንድንሞላ በሃይል እንጸልያለን።

ፕሬዘደንት ኔልሰን በሚያዝያ ወር ላይ እንዳስተማሩት፡ “በጎ አድራጎት የተፈጠርንበት አንዱ አካል በሚሆንበት ጊዜ፣ ሌሎችን የማዋረድ ያለን ግፊት ይቀንሳል። በሌሎች ላይ መፍረድን እንናቆማለን። ከሁሉም የህይወት ጎዳና ለመጡ ሰዎች ልግሥና ይኖረናል። ለሁሉም ሰው ልግሥና ማሣየት ለዕድገታችን አስፈላጊ ነው። ልግስና የአምላካዊ ባህሪ መሠረት ነው። ከበጎ አድራጎት ጎን ለጎን፣ ታማኝነትን፣ ትዕግስትን፣ ትጋትን ጨምሮ ሌሎች ከአዳኙ መንፈሳዊ ስጦታዎችን “ማዳበር፣ …፣ እና ማስፋፋት” እንፈልጋለን።

ኢየሱስ ክርስቶስን መምሰል ወደ አራተኛው ማመሳሰያ ይመራናል፦ ከዓላማው ጋር መዛመድ። በእርሱ ሥራ ላይ እንተባበራለን። እንደ ቀዶ ጥገና ሐኪም ዶ/ር። ኔልሰን መምህር፣ ፈዋሽ እና ተመራማሪ ታውቀው ነበሩ። በዶ.ር ሴልዝማን ቡድን ውስጠ የተጠቀመው የላፔል አርማ ማስተማርመፈወስ እናማግኘት የሚሉትን ቃላት በማሳየት እነዚህ ጥረቶች ላይ አጽንዖትን ይሰጣል። ለእኛ፣ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በራሳችን ላይ የመውሰድ አንዱ አካል በፈቃደኝነት፣ ሆን ተብሎ እና በጋለ ስሜት ግቦቻችንን ከእርሱ ጋር ማስማማትን ያካትታል። “ስንወድ፣ ስናካፍል እና ስንጋብዝ” በስራው ላይ እንቀላቀላለን። ሌሎችን ስናገለግል፣ በተለይ አቅመ ደካሞችን እና በምድራዊ ልምዳቸው የተጎዱትን፣ መንፈሳቸው ለተሰበረባቸው ወይም የተጨቆኑትን ስናገለግል ከእርሱ ስራ ጋር እንቀላቀላለን።

በመለየት፣ በማስታወስ፣ በመምሰል እና በአንድ መስመር በመሆን፣ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በይበልጥ በራሳችን ላይ እንወስዳለን። እነዚህን አራቱን ማድረግ ወደ አምስተኛው ማመሳሰያ ያመራናል—አቅምን መስጠት። በሕይወታችን የእግዚአብሔርን ኃይል እና በረከቶች እናገኛለን። የኔልሰን ፕሮፌሰርነት ማዕረግ የሚያቀርበው ለዶ/ር ሴልዝማን እውቅና እና ድጋፍ በእርሱ ብድን ውስጥ ባህሉን ለመለወጥ እንዲጠቀምበት ያደርጋል። ሌሎችን ለመርዳት ይህንን “የኃይል ስጦታ” ተግባር ላይ ያውላል። በተመሳሳይ መልኩ፣ የአዳኝን ስም በራሳችን ላይ ስንወስድ፣ የሰማይ አባታችን በስጋዊ ህይወት ውስጥ ተልእኳችንን እንድንፈጽም እንዲረዳን በእርሱ ሀይል ይባርከናል።

ከእግዚአብሔር ጋር ተጨማሪ ቃል ኪዳኖችን ስንገባ፣ የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በራሳችን ላይ በሙላት እንወስዳለን። በዚህም ምክንያት፣ እግዚአብሔር በተጨማሪ ኃይሉ ይባርከናል። ፕሬዘደንት ኔልሰን እንዳስተማሩት፡ “በጥምቀት ስፍራዎች እና በቤተመቅደሶች ውስጥ ቃል ኪዳኖችን የሚያደርግ —እና የሚጠብቃቸው—እያንዳንዱ ሰው ለኢየሱስ ክርስቶስ ሃይል የበለጠ አቅርቦት አለው። “ቃል ኪዳኖችን የመጠበቅ ሽልማት የሰማይ ሀይል ነው—ያም ሀይል መከራዎቻችንን፣ ፈተናዎቻችንን እና ከባድ ሀዘኖቻችንን በተሻለ ሁኔታ እንድንቋቋም ያጠነክረናል” በማለት ተናግረዋል።

ይበልጥ መንፈሳዊ ነገርን ተቀባይ እንሆናለን። የማይቻል የሚመስሉ ሁኔታዎችን ለመጋፈጥ ይበልጥ ድፍረት ይኖረናል። ኢየሱስ ክርስቶስን ለመከተል ባደረግነው ቁርጠኝነት ውሳኔ በይበልጥ እንበረታታለን። ስንተላለፍ በይበልጥ ፍጥነት ንስሐ እንገባለን እናም ወደ እርሱ እንመለሳለን። በኃይሉ እና በስልጣኑ ወንጌሉን ለማካፈል የተሻልን እንሆናለን። ፍርደኞች አናሳ አድርገን፣ የተቸገሩትን እንረዳቸዋለን። የኃጢአታችንን ስርየት እንይዛለን። የበለጠ ሰላም አለን እናም የበለጠ ደስተኛ እንሆናለን ምክንያቱም ሁል ጊዜ መደሰት እንችላለን። ክብሩም በዙሪያችን ይሆናል፣ መላእክቱም በላያችን ላይ ይጠብቁናል።

አዳኙ ይጋብዘናል፣ “ወደ አብ በስሜ ኑ፣ እናም በጊዜ ሙላቱ ተቀበሉ።” ይህን እንድታደርጉ አሳስባችኋለሁ። ወደ የሰማይ አባታችን ኑ። የኢየሱስ ክርስቶስን ስም በላያችን ላይ ውሰዱ። ከእርሱ ጋር ተቆጠሩ። ሁልጊዜ እርሱን አስታውሱ። እርሱ ለመሆን ጣሩ። እርሱን በስራው ላይ ተቀላቀሉ። በህይወታችሁ ውስጥ ኃይሉን እና በረከቱን ተቀበሉ። በፈቃደኝነት እና ሆን ብላችሁ ስሙን በልብችሁ አትሙት። ይህ በእግዚአብሔር ፊት “መቆም” ያስችላችኋል እናም እናንተን ለሚወክለው ለአዳኙ ጥብቅና ብቁ ያደርጋችኋል። በሰማያት ባለው በአባታችን መንግሥት ከፍ ያለ ወራሾች፣ ከበኩር ልጁ፣ ከተወደደው አዳኛችን እና ቤዛችን ጋር የጋራ ወራሽ ትሆናላችሁ።

እርሱ ህያው ነው። ይህን በእርግጥ አውቃለሁ። ይወዳችኋል። ህይወቱን ለእናንተ ሰጥቷል። በእርሱ በኩል ወደ አብ እንድትመጡ ይማጸናችኋል። በኢየሱስ ክርስቶስ ስም፣ አሜን።

ማስታወሻዎች

  1. እርዳታው እንደ ስጦታ ነው።

  2. አንድ ትኩረት የሚስብው የፕሬዘዳንት ኔልሰን ስኬታማው ስራቸው ለክፍት የልብ ቀዶ ጥገና የሚያገለግል የመጀመሪያው የልብ-ሳንባ ማለፊያ ማሽን መፍጠራቸው ነው።

  3. ፕሬዘደንት ኔልሰን እንደዘገቡት በቀዶ ሕክምና ልምዳቸው፣ በቀዶ ሕክምና ክፍል ውስጥ ያለ አንድ የቀዶ ጥገና ሀኪም ንዴቱን መቆጣጠር ተስኖት የኦፐራሲዮን ማድረጊያ ሰለት በፕሬዘደንት ኔልሰን እጅ ላይ ወረወረው። ፕሬዘደንት ኔልሰን እንዳሉት፥ “ይህ ተሞክሮ በእኔ ላይ ዘላቂ የሆነ ስሜት ትቶ አልፋል። በዚያው ሰዓት በእኔ የቀዶ ሕክምና ክፍል ውስጥ ማንኛውም ነገር ቢፈጠር ስሜቴን ከቁጥጥር ውጪ ፈጽሞ እንደማላደርግ ለራሴ ቃል ገባሁ። እኔም በዛን ቀን ምንም ነገር በንዴት እንደልወረውር ቃል ገባሁ—ኦፐራሲዮን ማድረጊያ ሰለትም ይሁኑ ወይም ደግሞ ቃላት” (“አስታራቂዎች ያስፈልጋሉ፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2023) (እ.አ.አ)፣ 98)።

  4. ልገሳው በፕሬዘደንት ራስል ኤም. ኔልሰን አስደናቂ የህክምና ስራ ወቅት ከተዘጋጁ የምርምር ወረቀቶች እና ሌሎች ሙያዊ ጽሑፎች ጋር ከ7,000 በላይ ስራ ላይ የዋሉ ዘገባዎችን አካቷል።

  5. የዩታ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንት፣ፕሬዘዳንት ቴይለር ራንዳልን ጨምሮ ፕሬዘዳንት ኔልሰንን የዩታ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዘዳንትን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ፕሬዘደንት ራስል ነልሰንን የተለየ ምሩቃን ሲሉ ጠቅሰዋል።

  6. ስነ ምግባር የሚለው ቃል “የአንድን ሰው፣ ቡድን ወይም ተቋም የሚለይ ባህሪን፣ ስሜትን፣ የሞራል ተፈጥሮን ወይም መመሪያን ይገልፃል” (Merriam-Webster.com Dictionary, “ethos”)።

  7. በ2018 (እ.አ.አ)፣ ባለቤቴ ሩት እና እኔ ዶ/ር ሴልዝማን ለኔልሰን ፕሮፌሰርነት በሚሾምበት ስነስርዓት ላይ ተገኝተን ነበር። በ2023 (እ.አ.አ)፣ ፕሬዚዳንት ኔልሰን የፕሮፌሽናል ወረቀቶቻቸውን ለዩታ ዩኒቨርሲቲ ሲለግሱ በመደበኛው ዝግጅት ላይ መገኘትም ችያለሁ።

  8. ሞሮኒ 7፥48ን ተመልከቱ።

  9. “መውሰድ” ተብሎ የተተረጎመው የዕብራይስጥ ቃል “የክርስቶስን ስም ውሰድ” በሚለው ሐረግ “ማንሳት” ወይም “መሸከም” ማለት ሲሆን ይህም አንድ ሰው ራሱን ከግለሰብ ወይም ከቡድን ጋር የሚያመለክት ባንዲራ እንደሚሰጥ ነው (see James Strong, The New Strong’s Exhaustive Concordance of the Bible [1984], Hebrew dictionary section, page 80, number 5375)።

  10. 2 ኔፊ 10፥24ሞሮኒ10፥32-33ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 76፥69ይመልከቱ።

  11. አልማ 37፥36

  12. ዶ.ር ሴልዝማን እንዲህ ሲሉ ተጠቅሰዋል፡- “ከፕሬዝዳንት ኔልሰን ጋር ስለ ጤና አጠባበቅ ማውራት ሲጀምሩ፣ ፊቱ ላይ የደስታ ስሜት ይንጸባረቃል። … ስለዚያ ሁሉ ነገር ሲናገር ምን ያህል ጉልበት እንዳለው ማየት በጣም የሚያስደንቅ ነው” (in Sydney Walker, “As President Nelson Turns 100, His Family and Associates Reflect on His Life and Legacy,” Church News, Sept. 7, 2024, thechurchnews.com)። እኔ በግሌ በፕሬዘደንት ራስል ኤም ኔልሰን አይኖች ውስጥ “የጤና እንክብካቤ ደስ የሚል መልክ” አይቻለሁ፣ ነገር ግን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲናገሩ ከሚያገኙት ብልጭታ ጋር ሲወዳደር ምንም አይደለም።

  13. ሞሮኒ 7፥47–48 ይመልከቱ።

  14. ራስል ኤም. ኔልሰን፣ “በእግዚአብሔር ፊት መተማመን፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2025 (እ.አ.አ)።

  15. 1 ቆሮንቶስ 12፥31ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 46፥8ን ተመልከቱ።

  16. ረስል ኤም. ኔልሰን “እስራኤልን በመሰብሰብ ውስጥ የእህቶች ተሳትፎ ፣“ሊያሆና፣ ፣ህዳር 2018 (እ.ኤ.አ) ፣ 69 ይመልከቱ ፡፡

  17. ወንጌሌን ስበኩ፦ የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል የማካፈል መመሪያ [2023 (እ.አ.አ)]፣ 123–38።

  18. ሙሴ 1፥39ተመልከቱ። የአሮናዊ ክህነት ስብሰባ ጭብጥ እንዲህ ይጀምራል፦ “እኔ የተወደድኩ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ፣ እናም እርሱ እንድሰራለት ሚፈልገው ስራ አለ” (የወንጌል ቤተመጻህፍት)። የወጣቶች ሴቶች ጭብጥ እንዲህ ይላል፦ “የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀመዝሙር እንደመሆኔ መጠን እንደ እርሱ ለመሆን እጥራለሁ። ግላዊ ራእይን እሻለሁ፣ በሱም መሰረት እተገብራለሁ እንዲሁም በተቀደሰ ስሙ ሌሎችን አገለግላለሁ (የወንጌል ቤተመጻህፍት)።

  19. ዲየትር ኤፍ ኡክዶርፍን፣ “የሚስዮናዊነት ሥራ፡ በልብህ ያለውን አካፍል፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2019 (እ.አ.አ) ተመልከቱ። ጌሪ ኢ. ስቲቨንሰን፣ “መውደድ፣ ማጋራት፣ መጋበዝ፣” ሊያሆና፣ ግንቦት 2022 (እ.አ.አ)፣ 84–87።

  20. በምድራዊ አገልግሎቱ መጀመሪያ ላይ፣ አዳኝ ከኢሳይያስ መዝገብ በመጥቀስ አላማውን ገልጾልናል፡- “የእግዚአብሔር መንፈስ በእኔ ላይ ነው፣ ለድሆች ወንጌልን እሰብክ ዘንድ ቀብቶኛልና፣ ልባቸው የተሰበረውን እንድፈውስ፣ ለታሰሩትም መዳንን እሰብክ ዘንድ፣ ለዕውሮችም ማየትን፣ [የተጎዱትን] ነጻ አወጣ ዘንድ”(ሉቃስ 4፥18–19).

  21. ወደ የሰማይ አባታችን የምናቀርበው ጸሎት እንኳን ይለወጣል። የመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት መግቢያ “ጸሎት” ላይ እንደተገለጸው፦ “ክርስቲያኖች በክርስቶስ ስም እንዲጸልዩ ተምረዋል። አእምሯችን የክርስቶስ አስተሳሰብ ሲሆን እና የክርስቶስ ምኞቶች—ቃሉ በእኛ ውስጥ ሲኖሩ በክርስቶስ ስም እንጸልያለን። ከዚያም እግዚአብሔር ሊሰጣቸው የሚችላቸውን ነገሮች እንጠይቃለን። ብዙ ጸሎቶች ሳይመለሱ ይቀራሉ ምክንያቱም እነዚህ በክርስቶስ ስም በፍፁም አይደሉም፤ የእርሱን አስተሳሰብ በምንም መንገድ አይወክሉም ነገር ግን ከሰው ልብ ራስ ወዳድነት ይወጣሉ።

  22. ትምህርት እና ቃል ኪዳን 109፥26 ተመልከቱ።

  23. ራስል ኤ. ኔልሰን፣ “አለምን ማሸነፍ እና እረፍትን ማግኘት፣” ሊያሆና፣ ህዳር 2022 (እ.አ.አ)፣ 96፤ አትኩሮት ተጨምሯል።

  24. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 109፥21–22 ተመልከቱ። “ሕዝብህ በበደል ጊዜ አንዳቸውም” የሚለው ሀረግ “መቼ” የሚለውን ቃል እንጂ “ምናልባት” የሚለውን አይጠቀምም። ይህ የሚያመለክተው አዳኝ ሁላችንም እንደምንተላለፍ፣ ስህተት እንደምንሰራ እና ኃጢአት እንደምንሰራ እንደሚገነዘብ ነው። ነገር ግን እቅዱ ቃል የተገባልንን “ወደ በረከቶች ለመመለስ” “በፍጥነት ንስሃ እንድንገባ” ነው።

  25. ዮሐንስ 16፥33ሞዛያ 4፥1118፥26አልማ 36፥2፣ 28–29ኤተር 7፥27ሞሮኒ 9፥25 ተመልከቱ።

  26. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 109፥22ን ተመልከቱ።

  27. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 93፥19

  28. ሞርሞን ክርስቶስ በሕይወታቸው ውስጥ ባልተሳተፈበት ጊዜ በሕዝቡ ላይ የሆነውን ገልጿል። ሕዝቦቹ “በአንድ ወቅት ደስ የሚያሰኙ ሕዝቦች ነበሩ፣ እናም ክርስቶስን እረኛቸው አድርገው ነበር፣ አዎን፣ በእግዚአብሔር አብ ተመርተው ነበር። ነገር ግን አሁንም እነሆ፣ ገለባ በነፋስ ፊት እንደሚወሰደው ወይም ሸራ እናም መሃለቁ ሳይኖራት ወይም ቀጽዘፊም እንደሌሉባት በሞገድ እንደምትናወጥ ጀልባ እነርሱም በሰይጣን ተመርተዋል፤ እናም እርሷም እንደዚህ እንደሆነች፣ እነርሱም ናቸው” (ሞርሞን 5፥17–18)። አዳኝ በህይወታችን ወስጥ መኖር ጋር፣ በኃይል፣ መረጋጋት እና መመሪያ ተባርከናል።

  29. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 109፥24

  30. ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 45፥3-5 ተመልከቱ።

  31. ሮሜ 8፥17 ተመልከቱ።