አሁንም እንዳይ
መፅሐፍ ሞርሞን በህይወቴ ውስጥ ያመጣው ተፅዕኖ በዚያ እውሩ ሰውዬ ላይ እንትፍ ተብሎ እና ጭቃ በዓይኖቹ ላይ እንደተደረገው ተዓምራዊ ስራ ያልተናነሰ ነበር።
ፕሬዘዳንት ኦክስ ስለ ፕሬዘዳንት ራሰል ኤም. ኔልሰን ህልፈት ያቀረቡትን ማስታወሻ ንግግር በማያበቃ ፍቅር ሁላችንም እናስተጋባለን። እናም በእኩል ፍቅር እና ጥልቅ ሃዘን፣ በሚሺጋን በቅርቡ እንዲሁም በየቀኑ በሚባል ሁኔታ በአለም ላይ የሚከሰቱትን እስከፊ ክስተቶችን ሁላችንም እናውቃለን። እነዚህን ነገሮች በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር እና እምነት እውቅናው አለን።
የዮሐንስ ምእራፍ ዘጠኝ ኢየሱስ እና ደቀ መዛሙርቱ ከመወለዱ ጀምሮ ዕውር በሆነ ለማኝ አጠገብ በኩል ሲያልፉም የነበረውን ሁኔታ ይዘግባል። ይህም ደቀ መዛሙርቱ የዚህ ሰው ገደብ ከየት እንደመጣ እና መተላለፊያውን በተመለከተ ኢየሱስን በርካታ ውስብስብ የሆኑ ሃይማኖታዊ ጥያቄዎችን እንዲጠይቁ አድርጓቸዋል። መምህሩ በጣም ቀላል እና በጣም የሚያስደንቅ ነገርን በማድረግ ምላሽ ሰጠ። ወደ መሬት እንትፍ አለና እና በምራቁም ጭቃ አድርጎ አነሳ። ከዚያም በጭቃው የዕውሩን ዓይኖች ቀባና፣ ሄዶም በሰሊሆም መጠመቂያ እንዲታጠብ ላከው። እነዚህን ሁሉ በመታዘዝ የፈጸመው እውሩ ሰውዬ እናም “ማየትም [ቻለ]፣” ቅዱስ መጽሐፍ። ከምኞት ወይም ክርክር አልፎ ተርፎም ከእውነት ጋር የሚቃረን ክፋት በተቃራኒ፣ ማስረጃ ምን ያህል አስፈላጊ ነው።
ይህ ተአምር ኢየሱስ አስቀድሞ አለን ብለው በሚያስቡት ሥልጣናቸው ላይ የጣለውን ሥጋት ይበልጥ ይጨመረዋል ብለው ፈሩ፣ የአዳኙ ጠላቶች አዲስ ማየት የቻለውን ሰው አግኝተው በቁጣ፣ “[ኢየሱስን] ይህ ሰው ኃጢአተኛ መሆኑን እኛ እናውቃለን አሉት።” ይህም ሰው ጥቂታ ካዳመጠ በኋላ፣ እርሱም መልሶ፣ “ኃጢአተኛ መሆኑን አላውቅም፤ [ነገር ግን] ዕውር እንደ ነበርሁ አሁንም እንዳይ ይህን አንድ ነገር አውቃለሁ“ አለ።
ኢየሱስ ስለዚህ ንግግር የመጀመሪያውን ትርጉም ገልጿል፣ ደቀ መዛሙርቱንም ሁሉም የተከሰተው “የእግዚአብሔር ሥራ በእርሱ እንዲገለጥ ነው እንጂ እርሱ ወይም ወላጆቹ ኃጢአት አልሠሩም” አላቸው። በዚህ ታሪክ ውስጥ ሁለት የአዳኙ ድርጊት መገለጹን አስታውሱ የዓይነ ስውሩን አይን “ቀባው” ይህም ድርጊት በመታጠብ የሚጠናቀቅ ነው። “የእግዚአብሔር ሥራ በእርሱ እንዲገለጥ ነው እንጂ” የሚለው አገላለጽ የስነስርዓትን መፈጸሙን የሚያመለክ ሊሆን ይችላል።
አንድ እውነት ስለመሆኑ ማስረጃ ሰማይን እና ምድርን የፈጠረው ፈጣሪ ይህን ተዓምር ለመስራት የተጠቀመውን መሳሪያን ነው፡ በምራቅ እና ጭቃ! እነዚህ የማይመስሉ ንጥረ ነገሮች እግዚአብሔር ሊባርከን ቢፈልግ ማንኛውንም ነገር ሊጠቀም እንደሚችል አዋጅ ናቸው። እንደ ንዕማን በዮርዳኖስ ወንዝ አልጠልቅም ብሎ እንዳግደረደረ ወይም እንደ እስራኤል ልጆች በበትሩ ላይ ያለውን የነሃሱን እባቡ ከማየት ቸል እንዳሉት፣ ወደ እርሱ የሚያጠቁመው መሳሪያ በሚያሳፍር ሁኔታ ተራ ስለሚመስለን የመቤዣችን ምንጭ የሆነውን በንቀት ቸል ማለት ምንኛ ቀላል ነው።
ነገር ግን ከመፅሐፈ ሞርሞን አንዳንድ ነገሮች ቀላል እና ውድ መሆናቸውን እና ኢየሱስ ከመወለዱ በፊት “መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት” እንደማይኖረው እንደተተነበየ አስታውሱ። አዲስ በተጠራች እና በተቸነቀች የሴቶች መረዳጃ ማህበር ፕሬዚዳንት ወይም ባለተማረ የ ኒው ዮርክ ልጅ ወይም በግርግም ውስጥ ባለ ህፃን በኩል እግዚአብሔር ግርማ ሞገስ ያለውን መልእክቱን ምን ያህል ጊዜ ልኳል።
የጸሎታችንስ መልሶች ባልተለመደ፣ ተራ፣ ወይም በተወሳሰበ መንገድ ቢመጡስ? ምንም እንኳ ለሂደቱ የቱንም ያህል ምራቅና ጭቃ ቢያስፈልግ በክርስቶስ ወንጌል ለመኖረ ፈቃደኞች ነን? ምን እየተደረገ እንደሆነ ወይም ለምን እንደሆነ ሁልጊዜም ግልጽ ላይሆንልን ይችላል፣ እናም ከጊዜ ወደ ጊዜ፣ ሁላችንም [በአባልነት] እንደ ቆየችው እህታችን ይሰማናል፣ “ጌታ ሆይ፣ በፈተና በህመም ያልተደበቀውንሽ በረከትህን እንዴት ነው ማገኘው?”
የሌላ ወነት መረጃን አስቡበት፣ ይህም ቅዱስ ክህነእትን በሚመለከት ነው። ጥንት አስቀድማ [ኢየሱስ ክርስቶስ] በተቋቋመችው ቤተክርስቲያን መዝገብ ውስጥ፣ የመጀመሪያው የሉቃስ መስመር ላይ እንዲህ ይነበባል፡ “አሥራ ሁለቱንም ደቀ መዛሙርት በአንድነት ወደ እርሱ ጠርቶ በአጋንንት ሁሉ ላይ ደዌንም ይፈውሱ ዘንድ ኃይልና ሥልጣን ሰጣቸው፤” ስጦታዎች አስደናቂ በሆኑ ማስረጃዎች ላይ ያልተመሰረቱ ደግሞም በባህላዊ ወይም በብኩርና ያልተወሰኑ ናቸው። በመንፈሳዊ ትምህርት ስልጠና ወይም በሥነ-መለኮትዊ ትምህርት ቤት የሚሰጡ አይደሉም። ስልጣኑን የሚሰጣቸው የመለኮታዊ ስልጣን ምንጭ ከሆነው ከጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ጀምሮ ባልተቋረጠ የስልጣን ቅደም ተከተል ባለው ሂደት መሰረት ስልጣንን ከያዘው እጅ በመጫን በተሰጠው ሰው እጆች ተጭኖባቸው ነው።
እናስ ስለምህረት ስጦታ በምትረዳው ቤተክርስቲያን ውስጥ እነዚህ በረከቶች እና ቃል ኪዳኖች ለሟች ዘመዶቻችን፣ ከእኛም በፊት ቀድመውን ላንቀላፉት ቤተሰቦቻችን ሲደርሱ ማየት አስደናቂ የቤተክርስቲያኗ እውነተኛነት ማስረጃ አይሆንም? ወንጌልን ማግኘት ባለመቻላቸው ወይም የተወለዱት መለኮታዊ ስነ ሥርዓቶች እና ቃል ኪዳኖች በማይገኙበት ጊዜ ወይም ቦታ ስለነበሩ [ቅድመ ዓያቶቻችን] ሊቀጡ ይገባቸዋልን? የኋለኛው ቀን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ለእነዚህም ሟች ለሆኑት፣ የማዳንን ስራ በድል የሚሰራበት እንዲሁም ለህያዋንም የአምልኮ እድሎችን እና ስነ ሥርዓቶችን የሚሰጥበት ቅዱስ፣ የተመረቀ የጌታ ቤቶች አሏት። በእኔ እውቀት፣ በዚህ ጉዳይ ላይ እውነትን ከምታሳይ ከአንድ ቤተክርስቲያን፣ እንዲሁም በየኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በስተቀር፣ እግዚአብሔር ለህያዋን እና ለሙታን ያለውን ዓለም አቀፋዊ ፍቅር የሚያሳይ ልዩ ማስረጃ በአለም ውስጥ በሌላ ቦታ አይታይም።
የመጀመርያው የእኔ እይታ፣ የእውነት እውነተኛ ማስረጃ የሆነው ሕይወት ሰጪ ግንኙነት ያገኘሁት ከተቀባ ሸክላ ወይም የሰሊሆም ገንዳ የመጣ አልነበረም። አይደለም፣ ከጌታ ፈውሴን ያመጣ የእውነት መሳሪያ በመፅሃፍ ውስጥ፣ አዎ፣ በመፅሐፈ ሞርሞን፦ ሌላኛው የኢየሱስ ክርስቶስ ምስክር ውስጥ በነበሩት ገጾች ነበር። ስለዚህ መጽሐፍ በአንዳንድ ከሓዲዎች ጥቃት ደርሶባቸዋል እና ውድቅ ተደርጎባቸው፣ ብዙውን ጊዜ ቁጣው ለተፈወሰው ሰው እንዳጋጠመው የሚያውቀውን ነገር ሊደርስበት እንደማይችል ከተናገሩት ሰዎች ጋር ይዛመዳል።
ይህ መጽሐፍ የተገኘበት መንገድ ተግባራዊ ሊሆን የማይችል፣ የማይታመን፣ አሳፋሪ፣ ሌላው ቀርቶ ቅድስና የጎደለው እንደሆነ በእኔ ላይ ተወርውሯል። ይህ መፅሐፍ የተገኘበትን መንገድ ያውቃል ብሎ ከሚገምት ሰው የሚናገረው ጨካኝ ንግግር ነው፤ ምክንያቱም እነዚህ ዘዴዎች የሚገለጹት መጽሐፉ “በአምላክ ስጦታና ኃይል” የተተረጎመ መሆኑ ብቻ እስከሆነ ድረስ ነው። ያ ነው። ያ ብቻ ነው። ይህም ቢሆን፣ መፅሐፍ ሞርሞን በህይወቴ ውስጥ ያመጣው ተፅዕኖ በዚያ እውሩ ሰውዬ ላይ እንትፍ ተብሎ እና ጭቃ በዓይኖቹ ላይ እንደተደረገው ተዓምራዊ ስራ ያልተናነሰ ነበር። ለእኔ የነፍሴ የደህንነት በትር፣ ወደላይ የሚሻገር እና ወደ ውስጥ የሚገባ የመገለጥ ብርሃን፣ የጨለማ ጭጋግ ሲመጣ መራመድ ያለብኝን መንገድ የሚያበራ ነው። እናም በእርግጥ እንደዛ አድርገዋል፣ ወደፊትም ያደርጋሉ።
እናም የአዳኝን ሁለንተናዊ ፍቅር እና የመቤዠት ጸጋን ከሰጠኝ እይታ አንጻር፣ አዲሱ የተባረከ ሰው ወላጆች ልጃቸው “እድሜ” ስለነበረው መሰማት አለበት ሲሉ በዚህ ጸድቄያለሁ፣ ምስክሬንም አካፍላችኋለሁ። እንግዲያውስ፣ እኔም እንደዚያ ነኝ። እርሱም አስተኩሮ በእነሱ ለመስማት እንዲገባው በእድሜ የገፋ ነበር። እንግዲያውስ፣ እኔም እንደዚያው ነኝ። 85ኛ ዓመቴን ለመያዝ ሁለት ወሮች ብቻ ናቸው የቀሩኝ። ከሞት ዳርቻ ሄጄ እናም ተመልሻለሁ። ከነገስታት እና ከንግስቶች፣ ነቢያት፣ ፕሬዳቶች እና ከሀዋሪያት ጋር አብሬ በእግር ተጉዤያለሁ። ከሁሉም በላይ፣ አንዳንድ ጊዜ በእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ተጥለቅልቄአለሁ። ምስክሬ እዚህ ጉዳይ ቢያንስ ግምት ውስጥ መግባት እንዳለበት አምናለሁ።
ወንድሞች እና እህቶች፣ የኋለኛው ቀን ቅዱሳን የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን በዳግም የተመለሰች እውነተኛ የአዲስ ኪዳን ቤተክርስቲያን—ከዚያም በላይ—እንደሆነች በሙሉ ነፍሴ አምናለው፣ ምክንያቱም የዚህች ዳግም መመለስ ማስረጃን ልክደው ስለማልችል ነው።። ሌሎች አሉኝ ብዬ ዛሬ የተናገርኳቸው ማስረጃዎች እውነት መሆናቸውን የሚያስረዱ፣ ከእነዚያ የመጀመሪያዎቹ ልምዶች ጀምሮ፣ በሺዎች—በመቶ ሺዎች የሚሆኑትን አግኝቻለሁን?—። ስለዚህ፣ አሁን በአይሁድ ጎዳናዎች ላይ ያለውን ወዳጄን በዝግተኛው ድምፄ በዝማሬ ብቀላቀለው ደስ ይለኛል፡
በኢየሱስ ክርስቶስ ስም፣ አሜን።