‘’በጋና የነበረ ‘እገዳ’፣ ’’ የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]
“በጋና የነበረ ‘እገዳ’፣፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
ሰኔ 1989–ህዳር 1990 (እ.አ.አ)
በጋና የነበረ ‘’እገዳ’’
ቅዱሳን መሰባሰብ ባልቻሉበት ሁኔታ በታማኝነት መቆየት
አሊስ ጆንሰን በሃገሯ ጋና ውስጥ ስታገለግል የነበረች ሚስዮናዊ ነበረች። እርሷ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መመስከር እና የኢየሱስ ክርስቶስን ቤተክርስቲያን ለማሳደግ መርዳትን ትወድ ነበር።
ቅዱሳን፣ 4፥416–17
አንድ ቀን፣ አሊስ አንድ የሚያናድድ ዜና ደረሳት። የጋና መንግስት ከዚህ በኋላ የቤተክርስቲያን ስብሰባዎች ሊካሄዱ አይቻሉም አለ። ሚስዮናውያን ከዚህ በኋላ ማስተማር አልቻሉም።
ቅዱሳን፣ 4፥417
የፖሊስ መኮንኖች ሚስዮናውያንን መኖሪያቸውን ትተው እንዲሄዱ አደረጓቸው እንዲሁም ቢስክሌቶቻቸውንም ወስዱባቸው። አንዳንድ አባላትም በእስር ቤት ተጥለው ነበር። ወታደሮች የቤተክርስቲያኗን ህንጻዎች ቆለፉ እናም ማንኛውንም ሰው አያስገቡም ነበር። ሰዎች ይህንን ‘’እገዳ’’ በማለት ጠርተውታል።
ቅዱሳን፣ 4፥417–18
ሚስዮናውያን ወደ ቤት መሄድ ነበረባቸው። አሊስ በሌላ ከተማ ከጓደኛዋ ጋር ለመኖር ሄደች። እርሷ ፈጽሞ ሚስዮኗን ለመጨረስ እንደማትችል በማወቋ ተጨነቀች።
ቅዱሳን፣ 4፥418
በጋና የነበሩ ቅዱሳን ግራ ተጋብተው፣ አዝነው፣ እናም ፈርተው ነበር። እነርሱ ምን መጥፎ ነገር እንዳደረጉ ባለማወቃቸው ግራ ተጋብተው ነበር። ዳግም እንደገና ወደ ቤተክርስቲያን መሄድ ይችሉ ይሆን?
ቅዱሳን፣ 4፥418
ምንም እንኳ በየቅርንጫፎቻቸው መሰባሰብ ባይችሉም፣ ቅዱሳን አሁንም ጌታን ይወዱ እና ሊያመልኩት ይፈልጉ ነበር። እነርሱ በየቤቶቻቸው የቅዱስ ቁርባን ስብሰባዎችን ያደርጉ ነበር። ክህነት የነበራቸው የቤተሰብ አባላት ዳቦውን እና ውሃውን ይባርኩ እናም ለቀሩት የቤተሰብ አባላት ያካፍሉ ነበር።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 6፥32፤ ቅዱሳን፣ 4፥419
ከወር እስከ ወር፣ እገዳው ቀጠለ። ቅዱሳን መዝሙሮችን ዘመሩ እናም በየቤታቸው ወንጌልን አንዳቸው ለአንዳቸው አስተማሩ። እምነታቸው ጸንቶ እንዲቆይ አንዳቸው አንዳቸውን ጎበኙ። ወደቤተክርስቲያን ተመልሰው በሚሄዱበት ወቅት ለመክፈል አስራታቸውን ለይተው አስቀመጡ። እገዳው እንዲያበቃም ጸለዩ እናም ጾሙ።
ቅዱሳን፣ 4፥436–37
በመጨረሻም፣ ከ18 ወራት በኋላ፣ መንግስት ቤተክርስቲያኗ እንደገና ስብሰባዎችን እንድታደርግ ወሰነ። በአሁኑ ጊዜ የኮሌጅ ተማሪ የነበረችውን አሊስን ለማናገር አዲሱ የሚስዮን ፕሬዚዳንት ጠየቀ። ‘’ከትምህርትሽ በኋላ ትመለሻለሽን እናም ሚስዮንን ታገለግያለሽን?’’ በማለት ጠየቀ። “አይ፣” በማለት መለሰች። ‘’እኔ አሁን ማገልገል ነው የምሻው!’’
ቅዱሳን፣ 4፥437–39
አሊስ እና ሌሎች ቅዱሳን ዳግም ወደቤተክርስቲያን ለመሄድ በመቻላቸው በጣም ተደስተዋል! ከእገዳው በኋላ በነበረው በመጀመሪያው እሁድ፣ አያሌ ሰዎች ምስክርነታቸውን መስጠት በመፈለጋቸው የቅዱስ ቁርባን ስብሰባው ለሁለት ሰአታት በሚሆን ያህል ተራዘመ። ጌታ እንዴት እንደባረካቸው እና እምነታቸው ጸንቶ እንዲቆይ እንደረዳቸው ተነጋገሩ።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 20፥75፤ ቅዱሳን፣ 4፥438