በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
የታላቅ ዋጋ ዕንቁ


“የታላቅ ዋጋ እንቁ፣” ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“የታላቅ ዋጋ እንቁ፣” ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

ሐምሌ 1835–መጋቢት 1842 (እ.አ.አ)

የታላቅ ዋጋ ዕንቁ

ከጌታ የመጣ ተጨማሪ ቅዱስ መጽሀፍ

ጆሴፍ ስሚዝ የግብጻውያንን ብራና እየተመለከተ።

አንድ ቀን፣ አንድ ሰው የግብጻውያንን ቅሪተ አካል ይዞ ወደ ከርትላንድ መጣ። ከቅሪተ አካሉ ጋር የተወሰኑ ብራናዎች፣ ወይም በጣም ያረጁ የወረቀት ጥቅልሎች ነበሩ። ብራናዎቹ በላያቸው ላይ የግብጻውያን ጽሁፍ ነበራቸው። ሰውየውም እነዚህን ለነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ አሳየው። ጆሴፍ በጽሁፎቹ በጣም ተማረከ።

Saints [ቅዱሳን]1፥219–20

ጆሴፍ ብራናውን ከኤማ ስሚዝ ጋር በጋራ ሲመለከቱ።

አንዳንድ ጓደኞቹ ቅሪተ አካሎቹን እና ብራናዎቹን በመግዛት ጆሴፍን ረዱት። ጆሴፍ ጽሁፎቹን ባጠና ጊዜ፣ ጌታ የመጽሐፍ ቅዱስ ነቢይ በነበረው በአብርሃም የተጻፉ ጥንታዊ ጽሁፎችን ገለጠለት። ኦሊቨር ካውድሪን በመሰሉ ጓደኞቹ አማካይነት፣ ጆሴፍ ጌታ ስለአብርሃም ትምህርቶች ያስተማረውን ጻፈ።

Saints [ቅዱሳን]1፥220

ጆሴፍ የአብርሃም እና የሰማዩ አባትን ራዕይ እያየ።

አብርሃም ከመወለዳችን በፊት ከሰማይ አባታችን ጋር ስለነበረን ህይወት ራዕይን አየ። እርሱም ኢየሱስ አዳኛችን ለመሆን የተመረጠ መሆኑን አየ። አብርሃም በተጨማሪ ስለ አለም አፈጣጠር ተማረ። ቅዱሳን እነዚህን ጽሁፎች ከአብርሃም በማግኘታቸው ተደስተዋል። ጌታ ሌሎች ተጨማሪ ነገሮችን ሊያስተምራቸው በመፈለጉ ደስተኞች ነበሩ።

አብርሃም 2፥6–113፥–5Saints [ቅዱሳን]1፥220

ጆሴፍ ከአብርሃም እና ከሙሴ ታሪኮች መነሳሳትን እየተቀበለ።

የአብርሃም ጽሁፎች የታላቅ ዋጋ እንቁ የተባለው የቅዱሳት መጽህፍት ክፍል አካል ሆነ። ይህ መጽሐፍ የሌላኛውን የመጽሐፍ ቅዱስ ነቢይ የሆነው የሙሴን ጽሁፎችም እንዲሁ የያዘ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ ያልተካተቱ እውነቶችን ያስተምራል። ጌታ ሰዎች እነዚህን እውነቶች እንዲያውቁ ይፈልጋል፣ በመሆኑም እነዚህን ለጆሴፍ ስሚዝ አካፍሎታል።

ሙሴ 1–8አብርሃም3፥1–5

አንድ ወጣት ወንድ እና ሴት የታላቅ ዋጋ እንቁን ሲያነቡ።

የታላቅ ዋጋ ዕንቁ ደግሞም የጆሴፍ ስሚዝን ምስክርነት እና 13ቱን የእምነት አንቀጾች ይዟል። ጆሴፍ ስሚዝ የኋለኞቹ ቀናት ቅዱሳን ምን እንደሚያምኑ ለአለም ለመናገር እነዚህን ነገሮች ጽፏል። እንቁ ትንሽ እንደሆነ ሁሉ፣ የታላቅ ዋጋ እንቁ ትንሽ መጽሀፍ ነው፣ ነገር ግን በጣም ውድ ነው።

የጆሴፍ ስሚዝ—ታሪክየእምነት አንቀጾች 1