በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ሉሲ ሞርሊ እና ቤተሰቦቿ


“ሉሲ ሞርሊ እና ቤተሰቦቿ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“ሉሲ ሞርሊ እና ቤተሰቦቿ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

ህዳር 1830 (እ.አ.አ)

ሉሲ ሞርሊ እና ቤተሰቦችዋ

ብዙዎች አመኑ እንዲሁም ተጠመቁ

ሉሲ ሞርሊ ሶስት ሚስዮናውያንን ወደ አቢግኤል ዳንኤልስ ቤት እየጋበዘች

አንድ ቀን፣ የ15 ዓመቷ ሉሲ ሞርሊ ጎረቤቷ አቢግኤል ዳኒልስን ልብስ ስትሠፋ እየረዳቻት ነበር። በሥራ ላይ እያሉም፣ በሩ ሲንኳኳ ሰሙ፡፡ ሶስት ሚስዮናውያን ነበሩ፡፡ አቢግኤል እንዲገቡ ጋበዘቻቸው። ኢየሱስ ክርስቶስ መልዕክት እንዲያካፍሉ እንደላካቸው ተናገሩ።

ቅዱሳን1፥102–3

ሚስዮናውያኑ ሉሲን እና አቢግኤልን ስለመፅሐፈ ሞርሞን እያስተማሩ።

ጆሴፍ ስሚዝ ነቢይ ይሆን ዘንድ ኢየሱስ እንደጠራው ሠዎቹ ለአቢግኤል እና ለሉሲ ነገሯቸው። በተጨማሪም፣ ስለመፅሐፈ ሞርሞን ነገሯቸው።

ቅዱሳን1፥103

አቢግኤል ሚስዮናውያን ቤቷን ለቀው እንዲወጡ እያደረገች።

አቢግኤል በመናደዷ ሉሲ ተገረመች። ሚስዮናውያን ቤቷን ለቀው እንዲወጡ አደረገች።

ቅዱሳን1፥103

ሉሲ ሚስዮናውያኑ ቤተሰቧን እንዲጎበኙ እየጠየቀቻቸው።

እነዚህ ሚስዮናውያን የእግዚአብሔር አገልጋዮች እንደሆኑ አውቃ ነበር። መንገዱ ላይ ያሉትን ቤተሰቦቿን እንዲጎበኙ ነገረቻቸው። “አባቴ የሚኖረው ከዚህ አንድ ማይል ርቀት ላይ ነው” አለቻቸው። “ወደዚያ ሂዱ ትመገባላችሁ እንዲሁም ይንከባከቧችኋል።”

ቅዱሳን1፥103–4

ሚስዮናውያኑ ከሉሲ እና ከቤተሰቧ ጋር ምግብ ተመገቡ።

ሉሲ ትክክል ነበረች። ሚስዮናውያኑ በሞርሊ ቤተሰብ እርሻ ውስጥ ጥሩ ምግብ ተመገቡ። የሉሲ ወላጆች የሲድኒ ሪግደን ጓደኞች ነበሩ። ኢየሱስ፣ ያሏቸውን ነገሮች ሁሉ ለሌሎች እንዲያካፍሉ እንደሚፈልግ ያምኑ ነበር። እነርሱን እና ጓደኞቻቸውን ያስተምሩ ዘንድ ሚስዮናውያኑን ጋበዟቸው።

ቅዱሳን1፥104

ሉሲ፣ አቢግኤል እና ሌሎችም እየተጠመቁ።

በዚያ ምሽት፣ እኩለ ሌሊት አካባቢ 17 ሰዎች ተጠመቁ። በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ፣ 50 ተጨማሪ ሰዎች ከሚስዮናውያን ለመስማት ወደ ሞርሊ እርሻ መጡ፣ ከዚያም መጠመቅ ይችሉ እንደሆነ ጠየቁ። የሉሲ ጓደኛ አቢግኤል ዳኒኤልስ እንኳ ስለ ሚስዮናውያን ያነበራትን ሀሳብ ቀይራ ነበር። እርሷና ባለቤቷ ቤተክርስቲያኗን ለመቀላቀል ወሠኑ።

ቅዱሣን1፥105ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 20፥25፣ 37