“ሐዋርያት በእንግሊዝ አገር ሚስዮን አገለገሉ” ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]
“ሐዋርያት በእንግሊዝ አገር ሚስዮን አገለገሉ” ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
ሐምሌ 1838–ሐምሌ 1841 (እ.አ.አ)
ሐዋርያት በእንግሊዝ አገር ሚስዮን አገለገሉ
በጌታ ቃል ኪዳን ማመን
ለጆሴፍ ስሚዝ በተሰጠ ራዕይ፣ ጌታ ሐዋርያትን ከውቅያኖስ ባሻገር ወደ እንግሊዝ አገር በሚስዮን እንዲያገለግሉ ይጠራቸዋል። ምንም እንኳን የሐዋርያት በጣም ርቀው መሄድ ከባድ ቢሆንበትም ጆሴፍ በጌታ ታመነ። ቤተሰቦቻቸውን ትተው መሄድ ለሐዋርያትም ከባድ ነበር። ነገር ግን ጌታ እንደሚባርካቸው ቃል ገባ።
ሒበር ሲ. ኪምባል እና ሚስቱ ቪላቴ ታዳጊ ቤተሰብ ነበራቸው። ከተወለደ አንድ ወር ብቻ የሆነ ልጅ ነበራቸው። ብዙዎቹ የቤተሰባቸው አባላት በጠና ታመው ነበር።
ቅዱሳን፣ 1፥405
ብሪገም ያንግም እንዲሁ ትምሞ ነበር፣ ቤተሰቡም ድሃ ነበረ። ነገር ግን የብሪገም ሚስት ሜሪ አን፣ “ሂድ እና በምስዮን አገልግል፣ እናም ጌታ ይባርክሃል” አለችው።
ቅዱሳን፣ 1፥404-5
ብሪገም መሄድ ጀመረ፣ ነገር ግን ወደ ሒበር ቤት በደረሰ ጊዜ፣ በጣም ደካማ ሆኖ መራመድ አቃተው። ከሒበር ቤተሰብ ጋር ለጥቂት ቀናት ቆየ።
ቅዱሳን፣ 1፥405
ብሪገም ደህና እንኪሆን እና እሱና ሒበር ተሽሏቸው እስኪሄዱ ድረስ ለመንከባከብ ሜሪ አን መጣች። ሁለቱም በጣም ቢደክሙም ወንጌልን ለመስበክ ፍላጎት ነበራቸው።
ቅዱሳን፣ 1፥405
ሒበር እና ብሪገም ሚስቶቻቸውን ተሰናብተው በሠረገላ ጀርባ ላይ ወጡ። በጣም የታመሙና ድሃ የሆኑ ቤተሰቦቻቸውን ትተው ሊሄዱ በመሆኑ ክፉኛ ተሰምቷቸው ነበር። ሰረገላው እየሄደ እያለ ሒበር ለብሪገም “ይህ በጣም ከባድ ነው” አለው። ቤተሰቦቻቸው ድፍረት እንዲሰማቸው ለመርዳት ፈለገ። ሒበር ሠረገላውን የሚነዳው እንዲያቆም ጠየቀው።
ቅዱሳን፣ 1:405–6
ቤት ውስጥ የነበረቸው ቪላቴ ድምጽ ሰማች። ሜሪ አን ወደቆመችበት በር መጣች። ሒበር እና ብሪገም ከሰረገላው ጀርባ ቆመው ኮፍያቸውን በአየር ላይ እያውለበለቡ አዩዋቸው እና “እንደሰት! እንደሰት! ለእስራኤል እንደሰት!” በማለት ጮሁ። ሴቶቹም “ደህና ሁኑ! እግዚአብሔር ይባርካችሁ!” በማለት መለሱ።
ቅዱሳን፣ 1፥406
በውቅያኖስ ላይ ረጅም ጉዞ ካደረጉ በኋላ ሒበር እና ብሪገም ወደ እንግሊዝ አገር ደረሱ። ከሌሎች ሐዋርያት ጋር፣ ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ እና ስለ ወንጌሉ ብዙ ሰዎችን አስተማሩ። በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተጠምቀው የአዳኙን ቤተክርስትያን ተቀላቀሉ።
ቅዱሳን፣ 1፥408–11
በእንግሊዝ አገር አገር ከተጠመቁ ሰዎች መካከል ብዙዎቹ ከተማዋን እና ቤተመቅደስን ለመገንባት ወደ ናቮ ሄዱ። እነሱ በሚስዮናዊ አገልግሎት ላይ ሳሉ ጌታ የሒበርን እና የብሪገምን ቤተሰብ እንደሚንከባከባቸው የገባውን ቃል ጠበቀ።
ቅዱሳን፣ 1፥437–39