“የማርቲንስ ቤተሰብ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]
“የማርቲንስ ቤተሰብ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
ሚያዝያ 1972–ህዳር 1978 (እ.አ.አ)
የማርቲን ቤተሰብ
የጌታን በረከቶች መጠባበቅ
ሄልቬሲዮ ማርቲንስ በሪዮ ዴ ዣኔሮ፣ ብራዚል ከስራ ወደቤት እየነዳ ይሄድ ነበር። መንገዱ በመኪኖች ተሞልቶ ስለነበር የትኞቹም መንቀሳቀስ አልቻሉም። ሄልቬሲዮ ስለህይወቱ አሰበ። እርሱ ጥሩ ስራ ነበረው። ባለቤቱን ሩዳን፣ እና ሁለት ልጆቹን፣ ማርከስን እና ማሪሳን ይወዳቸው ነበር። ነገር ግን እርሱ አንዳች ነገር እንደጎደለው ተሰምቶታል።
ቅዱሳን፣ 4፥229–30
ሄልቬሲዮ ከመኪናው ወጥቶ ይጸልይ ጀመረ። እርሱም ‘’አምላኬ ሆይ፣’’ አለ፣ ‘’የት እንደሆንክ አላውቅም፣ ነገር ግን የሆነ ቦታ እንዳለህ አውቃለሁ።’’ ቤተሰቡ አንድን ነገር እየፈለገ እንደሆነ እና የእርሱን እርዳታ እንደሚሹ ለሰማይ አባት ነገረ። ከዚያም ሄልቬሲዮ ወደ መኪናው ተመለሰ እና ወደ ቤቱ እየነዳ ሄደ።
ቅዱሳን፣ 4፥230
በኋላም፣ ጌታ ከዩናይትድ ስቴትስ ሚስዮናውያንን ላከ። እነርሱም የማርቲንስን ቤተሰብ ጎበኙ። ሄልቬሲዮ እነርሱ ወደቤቱ ሰላማዊ መንፈስን እንዳመጡለት መገንዘብ ቻለ። በወቅቱ፣ ጥቁር የቆዳ ቀለም የነበራቸው ሰዎች በአሜሪካ ውስጥ አብዛኛውን ጊዜ በመልካም እየታዩ እንዳልሆነ አወቀ። እንዲህም በማለት ጠየቀ፣ ‘’የእናንተ ሃይማኖት ጥቁሮችን እንዴት ይመለከታቸዋል?’’
ቅዱሳን፣ 4፥230–31
ሚስዮናውያን ሁሉም የእግዚአብሔር ልጆች መጠመቅ እንደሚችሉ ገለጹ። ነገር ግን፣ በዚያን ጊዜ፣ የአፍሪካ ዝርያ ያላቸው ጥቁር ህዝቦች ክህነትን እንዲያገኙ ወይም የቤተመቅደስ ስርዓቶች ውስጥ እንዲሳተፉ አልተፈቀደላቸውም ነበር። ሄልቬሲዮ እና ሩዳ ሌሎች ተጨማሪ ጥያቄዎች ነበሯቸው። ሚስዮናውያኑ ጥያቂዎቹን ለመመለስ የተቻላቸውን ሁሉ አደረጉ።
ቅዱሳን፣ 4፥231
ለአያሌ ዓመታት፣ ነቢያት የክህነት እና የቤተመቅደስ በረከቶች ለሁሉም ህዝቦች መቼ መሰጠት እንዳለባቸው ጸልየዋል።
ቅዱሳን፣ 4፥71
ሄልቬሲዮ እና ሩዳ ወደ ቤተክርስቲያን ለመሄድ ሙከራን ለማድረግ ወሰኑ። በዚያ የነበሩ ቅዱሳን አፍቃሪ እና ደግ ነበሩ። የማርቲንስ ቤተሰብ በቤተክርስቲያን የተማሯቸውን ነገሮች ወደዋቸዋል።
ቅዱሳን፣ 4፥231–32
አንድ ቀን፣ ከቤተክርስቲያን ወደ ቤት ሲመለሱ፣ ማርከስ ደስተኞች መስለው እንደሚታዩ ለቤተሰቡ ነገራቸው። ማርከስም ‘’ይህንን ምን እየፈጠረው እንዳለ አውቃለሁ’’ አለ። ‘’የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል።’’ የተቀሩት የቤተሰቡ አባላት ማርከስ ትክክል እንደነበር አውቀዋል። ለመጠመቅ እና የመንፈስ ቅዱስ ስጦታን ለመቀበል ወሰኑ።
ቅዱሳን፣ 4፥232
ከዓመታት በኋላ፣ በብራዚል የነበሩ ቅዱሳን ቤተመቅደስን በመስራት ተጠምደው ነበር። የማርቲንስ ቤተሰብ ተደስተው ነበር፣ ነገር ግን ደግሞ በጣም አዝነው ነበር። ከተመረቀ በኋላ ወደ ቤተመቅደሱ ለመግባት እይችሉም ነበር። ‘’አትጨነቂ፣’’ በማለት ሄልቪሲዮ ለሩዳ ነገራት። “ጌታ ሁሉን ያውቃል።’’
ቅዱሳን፣ 4፥293–94
በታማኝነት መቆየት ቀላል አልነበረም። ሰዎች በማርቲንስ ቤተሰብ ላይ ይቀልዱ ነበር። ጓደኖቻቸው እንኳን ለምን በቤተክርስቲያኑ አባልነት እንደቆዩ ሊረዱ አልቻሉም ነበር። ነገር ግን ሄልቪሲዮ እና ቤተሰቡ ይህ የኢየሱስ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን መሆኑን አውቀው ነበር።
ቅዱሳን፣ 4፥251–52
አንድ ቀን፣ ሄልቪሲዮ ከስራ ወደቤት በመጣ ጌዜ፣ ሩዳ እንዲህ አለችው፣ ‘’አንድ፣ አስገራሚ ዜና አለኝ!’’ ከብዙ ጾም እና ጸሎት በኋላ፣ ነቢዩ፣ ፕሬዚዳንት ስፔንሰር ደብሊው. ኪምቦል፣ ራእይን ተቀበሉ። ማንም፣ የቆዳ ቀለሙ ምን ይሁን ምን፣ የክህነትን እና የቤተመቅደስን ሁሉንም በረከቶች ሊያገኝ እንደሚችል እግዚአብሔር ነገራቸው።
አስተዳደራዊ አዋጅ 2፤ ቅዱሳን፣ 4፥318–19
የማርቲንስ ቤተሰብ እና ሌሎች ብዙዎች ለረዥም ጌዜ ጠብቀው ነበር። አሁን መጠበቁ አበቃ! ሄልቪሲዮ እና ማርከስ ክህነትን ተቀበሉ። ሄልቪሲዮ፣ ሩዳ፣ እና ልጆቻቸው እንደቤተሰብ በቤተመቅደስ በአንድነት ተሳሰሩ። አሁን እነርሱ የወንጌልን በረከቶች ሁሉ መቀበል ይችላሉ።
ቅዱሳን፣ 4፥319–21