“ከአንድ በላይ ሚስቶችን ማግባት፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]
“ከአንድ በላይ ሚስቶችን ማግባት፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
1831–1890 (እ.አ.አ)
ከአንድ በላይ ሚስቶችን ማግባት
ለተወሰነ ጊዜ የተሰጠ ትእዛዝ
ነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ መጽሐፍ ቅዱስን እያጠና ሳለ፣ ከአንድ በላይ ሚስቶችን አግብተው ስለነበሩት ነቢያት እንደ አብርሃም እና ሙሴ የመሳሰሉትን አነበበ። ጆሴፍ ስሚዝ አያሌ ጥያቄዎች ነበሩበት። ስለዚህ ለመጸለይ እና ጌታን ለመጠየቅ ወሰነ።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 132፥1፤ ቅዱሳን፣ 1፥121፣ 503
ጌታም አብዛኛውን ጊዜ አንድ ሰው አንዲት ሚስት ብቻ ሊኖረው እንደሚገባ ተናገረ። ነገር ግን አንዳንድ ጊዜ ጌታ አንድን ሰው ከአንድ በላይ ሚስት እንዲኖረው አድርጓል። ይህም ከአንድ በላይ ሚስቶችን ማግባት ይባላል። ጌታ ሲያዛቸው ብቻ የእርሱ ሰዎች ከአንድ በላይ ሚስት እንደሚኖራቸው ለጆሴፍ ነግሮታል።
ያእቆብ 2፥27–30፤ ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 132፥34–15፤ ቅዱሳን፣ 1፥121፣ 290–91፣ 489–90፣ 503
ከዓመታት በኋላ፣ ጌታ ለጆሴፍ እና ለሌሎች ቅዱሳን ከአንድ በላይ ሚስቶች እንዲኖሯቸው ነገራቸው። በዚህ ትእዛዝ መኖር ቀላል አልነበረም።
ቅዱሳን፣ 1፥290–91፣ 444–46
መንግስትም ከአንድ በላይ ሚስት ማግባትን በመቃወም ህጎችን አወጣ። አንዳንድ ቅዱሳን፣ የቤተክርስቲያን መሪዎችን ጨምሮ፣ ወደ እስር ቤት ተጣሉ።
ቅዱሳን፣ 2፥501–4
በ1890፣ ጌታ የቤተክርስቲያኗ ፕሬዚዳንት ለነበሩት ለውልፈርድ ውድረፍ፣ ማንም ሰው ከዚህ በኋላ ከአንድ በላይ ሚስቶች ሊኖሩት እንደማይገባ ነገረ። የቤተክርስቲያኗ መሪዎች ይህንን ትእዛዝ ለቅዱሳን አካፈሉ። ዛሬም ይህ የጌታ ትእዛዝ ነው—አንድ ወንድ አንዲትን ሴት ብቻ ሊያገባ ይገባል።
አስተዳደራዊ አዋጅ 1; ቅዱሳን፣ 2፥598–601፣ 607–9