“ሳሙኤል ስሚዝ መፅሐፈ ሞርሞንን አጋራ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች (2024 [እ.አ.አ])
“ሳሙኤል ስሚዝ መፅሐፈ ሞርሞንን አጋራ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
1830–1832 (እ.አ.አ)
ሳሙኤል ስሚዝ መፅሐፈ ሞርሞንን አጋራ
አንድ መፅሐፍ የብዙዎችን ሕይወት ባረከ
ጌታ የጆሴፍን ታናሽ ወንድም ሳሙኤል ስሚዝን ወንጌልን ለማካፈል ወደ ሚስዮን እንዲሄድ ጠራው። ሳሙኤል ጆንን እና ሮዳ ግሪንን አገኛቸው ስለመፅሐፈ ሞርሞንም ነገራቸው። ጆን የሌላ ቤተክርስቲያን ሰባኪ ነበር። የመጽሐፉን ቅጂ ወስዶ በእርሡ ቤተክርስቲያን ውስጥ ሊያነበው የሚፈልግ ሰው ካለ ለማየት እንደሚፈልግ ተናገረ።
ቅዱሳን፣ 1፥99
ከጥቂት ወራት በኋላ ሳሙኤል ተመልሶ መጣ። ሮዳ ባለቤቷ መፅሐፈ ሞርሞንን ለማንበብ የሚፈልግ ሰው ሊያገኝ እንዳልቻለ ተናገረች። ለሳሙኤልም መልሳ ሠጠችው።
ቅዱሳን፣ 1፥99
ሳሙኤል አዝኖ ነበር። ለመሄድ ፊቱን አዞረ ሮዳ ግን አስቆመችው። መጽሐፈ ሞርሞንን እንዳነበበችውና እንደወደደችው ተናገረች።
ቅዱሳን፣ 1፥99
መንፈስ ቅዱስ፣ መጽሐፉን ለሮዳ መልሶ እንዲሠጣት ለሳሙኤል ነገረው። ሳሙኤልም “ምስክርነት እንዲሰጥሽ እግዚአብሔርን ለምኚ” አላት። ስለመንፈስ ቅዱስ እና መፅሐፈ ሞርሞን እውነት ስለመሆኑ እንዴት እንደምታውቅ ሮዳን አስተማራት።
ሞሮኒ 10፥3–5፤ ቅዱሣን፣ 1፥99-100
ሳሙኤል ከሚስዮን ወደ ቤቱ ተመለሰ። ማንንም አላጠመቀም ነበር፤ እንዲሁም ለመፅሐፈ ሞርሞን ፍላጎት ያሳዩት ጥቂት ሰዎች ብቻ ነበሩ።
ሮዳ እና ጆን ፀለዩ፤ መንፈስ ቅዱስም መፅሐፈ ሞርሞን እውነት መሆኑን ነገራቸው። ከዚያም፣ ሮዳ መጽሐፉን ለወንድሟ ለብሪገም ያንግ አካፈለች።
ቅዱሳን፣ 1፥100
ብሪገም እና ጓደኛው ሄበር ኪምባል የኢየሱስን እውነተኛ ቤተክርስቲያን እየፈለጉ ነበር። መፅሐፈ ሞርሞንን አነበቡ። ለሁለት ዓመታት ያህል የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል አጠኑ እንዲሁም ጸለዩ።
በዚህ ጊዜ ብሪገም እና ሄበር ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ቤተክርስቲያን ስብሰባዎች ይሄዱ ነበር። ከእነዚህ ስብሠባዎች በአንዱ፣ ብሪገም አንድ ሚስዮናዊ ምስክርነቱን ሲያካፍል ሠማ። ሚስዮናዊው ታላቅ ተናጋሪ አልነበረም፤ ሆኖም በተናገረበት ጊዜ ብሪገም መንፈስ ቅዱስ ተሰማው። እውነቱን እየተናገረ እንደነበረ ብሪገም አውቆ ነበር።
ብሪገም፣ ሄቤር እና ሚስቶቻቸው፣ ሚርያም እና ቨሌት፣ ተጠመቁ። አዳኙን እና ወንጌሉን ወደዱ። ከዓመታት በኋላ፣ ጌታ ብሪገምን እና ሄበርን ሐዋርያቱ እንዲሆኑ እና በሚስዮን እንዲያገለግሉ ጠራቸው። ሳሙኤል መጽሐፈ ሞርሞንን በማካፈሉ፣ ብዙ ሰዎች የአዳኙን ቤተክርስቲያን ተቀላቀሉ።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 124፥127–29፤ 126፤ ቅዱሳን፣ 1፥215–16