በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ወደ ኦሃዮ መሰባሰብ


“ወደ ኦሀዮ መሰባሰብ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“ወደ ኦሀዮ መሰባሰብ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

ታህሳስ 1830–ግንቦት1831 (እ.አ.አ)

ወደ ኦሃዮ መሰባሰብ

የሉሲ ስሚዝ እምነት እና ተአምር

ሉሲ ስሚዝ እና የቤተሰብ አባላት ወደ ኦሀዮ ለመዛወር ሲዘጋጁ።

በኦሀዮ፣ የበለጠ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ወደ ቤተክርስቲያኗ እየተቀላቀሉ ነበር። በሌሎች ስፍራዎች እየኖሩ ያሉ ቅዱሳን በኦሀዮ መሰባሰብ እንዳለባቸው ጌታ ለጆሴፍ ስሚዝ ነገረው። ይህም ረዥም ጉዞ ይሆናል። ነገር ግን ከተሰባሰቡ በኋላ፣ ለቅዱሳን ህጉን እንደሚያስተምራቸው እና ይሰሩ ዘንድ በሀይሉ እንደሚባርካቸው ጌታ ቃል ገባላቸው።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 3738፥32Saints [ቅዱሣን]1፥109–110

ሉሲ እና ሌሎች ተጓዦች ወደ ኦሀዮ ለመሄድ ወደ ጀልባ ሲወጡ።

የጆሴፍ እናት፣ ሉሲ፣ እና ወደ 80 የሚሆኑ የቤተክርስቲያን አባላት በኒውዮርክ ያለ ቤታቸውን ትተው ወደ ኦሃዮ ተዘዋወሩ። የጉዞአቸውን የተወሰነ እርቀት ወደሚወስዳቸው ጀልባ ውስጥ ገቡ። ለጥቂት ቀናት ከተጓዙ በኋላ፣ ጀልባው መቆም ነበረበት። በውሃ ውስጥ የነበረ ግግር በረዶ መንገዳቸውን ገታባቸው።

Saints [ቅዱሳን]1፥121–22

ጀልባው በወደቡ ውስጥ በበረዶ ተገታ።

በረዶው እስኪሰባበር ቅዱሳኑ መጠበቅ ነበረባቸው። ደክሟቸው፣ ርቧቸው፣ ረጥበው፣ እና በርዷቸው ነበር።

Saints [ቅዱሳን]1፥122

የተወሰኑ ቅዱሳን ትግስታቸው አልቆ እንዲሁም መጨቃጨቅ ጀምረው ነበር።

መጠበቁ ከባድ ነበር። የተወሰኑ ቅዱሳን እርስ በርሳቸው መጨቃጨቅ ጀምረው ነበር።

Saints [ቅዱሳን]1፥122

ሉሲ በወደቡ ውስጥ ያለውን በረዶ እንዲያቀልጠው ወደ እግዚአብሔር እንዲጸልዩ ለቅዱሳኑ ነገረች።

ሉሲ ቅዱሳን ሲጨቃጨቁ መስማቷን አልወደደችውም። አንድ ነገር መናገር እንዳለባት አውቃለች። “እምነታችሁ ወዴት አለ?” በማለት ጠየቀች። ወደ እግዚአብሔር ቢጸልዩ፣ መንገዳቸውን ይቀጥሉ ዘንድ እርሱ በረዶውን እንደሚሰብርላቸው ሉሲ ለቅዱሳኑ ተናገረች።

Saints [ቅዱሳን]1፥122–23

በበረዶው ውስጥ የተከፈተ መንገድ።

በድንገት፣ በረዶው ለሁለት ሲከፈል እንደ መብረቅ ያለ ድምጽ ሰሙ። በበረዶው ውስጥ መንገድ ተከፈተ፣ ይህም ጀልባቸው ሊያልፍ የሚችልበት በቂ ስፋት ያለው ነበር።

Saints [ቅዱሳን]1፥123

ቅዱሳን የሰማይ አባትን ለማመስገን ተሰባስበው።

ቅዱሳኑ ተገርመዋል እንዲሁም አመስጋኞች ነበሩ። ቅዱሳን የሰማይ አባትን ለማመስገን ለጸሎት ተሰበሰቡ። ጀልባቸው በሰላም ወደ ኦሀዮ ተጓዘ።

Saints [ቅዱሳን]1፥123

ቅዱሳን በኦሃዮ በሰላምታ ተቀባይነት አገኙ።

ቅዱሳን በኦሀዮ ሲደርሱ፣ የቤተክርስቲያኗ አባላት በሠላምታ ተቀበሏቸው እና የሚኖሩበትንም ስፍራ በመፈለግ አገዟቸው። ጌታ ለቅዱሳን ህጉን እንደሚያስተምራቸው እና ይሰሩ ዘንድ በሀይሉ እንደሚባርካቸው የገባላቸውን ቃል ጠብቋል።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 42Saints [ቅዱሳን]1፥126