በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
የሴቶች መረዳጃ ማህበር


“የሴቶች መረዳጃ ማህበር” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“የሴቶች መረዳጃ ማህበር” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

መጋቢት 1842 (እ.አ.አ)

የሴቶች መረዳጃ ማህበር

የናቩ ሴቶች ጌታን ያገለግላሉ

ማርጋሬት ኩክ እና ሳራ ኪምባል በናቩ ስለሚገነባው አዲሱ ቤተመቅደስ እያወሩ።

ማርጋሬት ኩክ በናቩ ትኖር ነበር። በልብስ ስፌት እየረዳች ለሣራ ኪምባል ትሰራ ነበር። እሷ በምትሠራበት ጊዜ በናቩ ስለሚገነባው አዲሱ ቤተመቅደስ ማውራት ይወዱ ነበር። ስለ ቤተመቅደሱ ጓጉተው ነበር።

ቅዱሳን1፥447

ማርጋሬት የቤተመቅደሱ ሰራተኞች ያረጀ ልብስ እንደሚለብሱ አስተዋለች።

አንድ ቀን፣ ማርጋሬት ቤተመቅደሱን ከሚገነቡት ወንዶች መካከል ብዙዎቹ ያረጀ እና የተቀዳደደ ልብስ እንደሚለብሱ አስተዋለች። እሷ እና ሳራ በአንድነት ለወንዶች አዲስ ሸሚዞችን መስፋት ይችሉ እንደሆነ አሰበች። ሳራ ሃሳቡን ወደደችው። እሷ እና ማርጋሬት ሰራተኞቹን ለመርዳት ቡድን ስለማቋቋም ከሌሎች ሴቶች ጋር ተነጋገሩ።

ቅዱሳን1፥447–48

ጆሴፍ ስሚዝ ከማርጋሬት፣ ሳራ እና ሌሎች ጋር የቤተክርስቲያኗ መረዳጃ ማህበርን ለመመስረት ሲገናኝ።

ነቢዩ ጆሴፍ ጌታ በሃሳባቸው ደስተኛ እንደሆነ እና ለእነርሱም የተሻለ ነገር እንዳለው ተናገረ። ጆሴፍ ሴቶቹ በመጋቢት 17 ቀን 1842 (እ.አ.አ) ከእሱ ጋር እንዲገናኙ ጋበዛቸው። የክህነት ስልጣንን በመጠቀም የቤተክርስቲያኗን ሴቶች አደራጀ። ቡድናቸውን የናቩ የሴቶች መረዳጃ ማህበር ብለው ለመጥራት ወሰኑ።

ቅዱሳን1፥448450–51

ማርጋሬት ከሁለት ሴቶች ጋር ስትነጋገር።

የሴቶች መረዳጃ ማህበር ሰዎችን ለቤተመቅደስ እና ለዘለአለም ህይወት በረከቶች እንዲዘጋጁ እንዲረዱ ጆሴፍ ጠየቃቸው። ኢየሱስን የመከተል ምሳሌ መሆን አለባቸው።

ቅዱሳን1፥451

የሴቶች መረዳጃ ማህበር አባላት ለተቸገረ ቤተሰብ ምግብ እያመጡ።

በተጨማሪም የሴቶች መረዳጃ ማህበር ድሆችን ፈልጎ በማግኘት መርዳት እንደሚገባቸ ተናገረ። ድሆች የነበሩ ሴቶች እንኳን የተቸገሩ ሰዎችን መርዳት ይፈልጉ ነበር።

ቅዱሳን1፥449

የሴቶች መረዳጃ ማህበር እየተደራጀ።

የሴቶች መረዳጃ ማህበር ተደራጀ። ኤማ ስሚዝ ፕሬዚዳንት እንድትሆን ተጠራች። ሁለት አማካሪዎች ሣራ ክሊቭላንድ እና አን ውትኒን ጠራች። በተጨማሪም እላይዛ አር. ስኖው ፀሐፊ እንድትሆን ጠራች።

ቅዱሳን1፥450

በሴቶች መረዳጃ ማህበር ውስጥ ኤማ ስታስተምር።

ጌታ ኤማ ጥሪዋን እንድትፈጽም ረዳት። ኤማ በጌታ አገልግሎት ውስጥ ሴቶች ታላቅ ነገር ማድረግ እንደሚችሉ አስተማረች። እያንዳንዳቸውም መልካም ለማድረግ መንገዶችን እንዲፈልጉ ፈለገች። ከሁሉም በላይ ደግሞ ልክ እንደ ኢየሱስ ሌሎች ሰዎችን መውደድ እንዳለባቸው ነገረቻቸው። በናቩ የሚኖሩ ብዙ ሴቶች የሴቶች መረዳጃ ማህበሩን ተቀላቀሉ።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 25፥37፣ 7ቅዱሳን1፥451

በቤተክርስቲያኗ ውስጥ ያሉ ሴቶች በአለም ዙሪያ ያሉትን ሰዎች እንዴት እንደረዱ የሚያሳይ ምስል ስብስብ።

እነርሱም ሰዎች ለቤተመቅደስ በረከቶች እንዲዘጋጁ አግዘዋል እንዲሁም በናቩ ውስጥ የተቸገሩ ብዙ ቤተሰቦችን ረድተዋል። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በዓለም ዙሪያ ያሉ ሴቶች የሴቶች መረዳጃ ማህበርን ተቀላቅለዋል። ሰዎችን ማገልገላቸውን እና የቤተመቅደስ በረከቶችን እንዲቀበሉ መርዳት ቀጥለዋል።

ቅዱሳን1፥451