በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ሜሪ እና ካሮሊን ሮሊንስ


“ሜሪ እና ካሮሊን ሮሊንስ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“ሜሪ እና ካሮሊን ሮሊንስ፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

ህዳር 1830(እ.አ.አ)—ሐምሌ 1831 (እ.አ.አ)

ሜሪ እና ካሮሊን ሮሊንስ

ለቅዱሳት መጻህፍት ብርቱ ፍቅር

ሜሪ ሮሊንስ ሚሲዮናውያን ስለመፅሐፈ ሞርሞን ሲናገሩ ትሰማለች።

ማሪ ሮሊንስ ሚስዮናውያን ከርትላንድ፣ ኦሃዮን ሲጎበኙ 12 አመቷ ነበር። ስለመፅሐፈ ሞርሞን ሲናገሩ ሰማቻቸው። በዚያን ጊዜ፣ በከርትላንድ ውስጥ አንድ የመፅሐፈ ሞርሞን ቅጂ ብቻ ነበር፣ እና አይዛክ ሞርሊ የሚባል የቤተክርስቲያን መሪ የነበረው ሰው ይዞት ነበር።

ሜሪ መጽሐፈ ሞርሞንን ለመዋስ ስትጠይቅ።

ሜሪ ወደ ወንድም ሞርሊ ቤት አመራች እና መፅሐፉን ለማየት ጠየቀች። ወንድም ሞርሊም እንድትይዘው አደረጋት። ሜሪ ወደ ቤቷ ይዛው መሄድ ትችል እንደሆነ ጠየቀች።

ሜሪ መጽሐፈ ሞርሞንን ለመዋስ ስትማጸን።

ወንድም ሞርሊ የእርሱን የመጽሐፍ ቅጂ ለመስጠት ፈቃደኛ አልነበረም። እርሱ ብዙውን ክፍል አላነበበም ነበር። ሜሪ መጽሐፉን እንዲያውሳት ወንድም ሞርሊን ተማጸነች።

ሜሪ መፅሐፈ ሞርሞንን እያነበበች።

ወንድም ሞርሊም ተስማማ። እርሱም በሚቀጥለው ቀን በጊዜ መልሳ የምታመጣ ከሆነ መጽሀፉን ወደ ቤቷ ይዛ መሄድ እንደምትችል ነገራት። ሜሪ እንደ ሀብት ቆጠረችው። እርሷም አብዛኛውን ሌሊት በማንበብ አሳለፈች።

ሜሪ መፅሐፉን ለአይዛክ ሞርሊ ስትመልስ።

ሚሪ መጽሐፉን በመለሰች ጊዜ፣ ወንድም ሞርሊ ባነበበችው ብዛት ተገረመ። ‘’ልጄ ሆይ፣’’ እርሱም አለ፣ ‘’ይህን መጽሀፍ ወደ ቤትሽ ወስደሽ ጨርሽው። እኔ ልጠብቅ እችላለሁ።’’

ሜሪ ከጆሴፍ ስሚዝ ጋር እየተገናኘች።

ሜሪ በከርትላንድ መጽሐፉን ሙሉ ለሙሉ ያነበበች የመጀመሪያ ሰው ነበረች። ካነበበችውም በኋላ፣ ከነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ ጋር ተገናኘች። እርሱም ሜሪ ምን ያህል መጽሐፈ ሞርሞንን እንደምትወድ ባወቀ ጊዜ የወንድም ሞርሊን ቅጂ ልትወስድ እንደምትችል ነገራት። ለወንድም ሞርሊ ሌላ እንደሚሰጠው ተናገረ።

ሜሪ የትእዛዛቱ መጽሐፍ ሲታተም ትመለከታለች።

በዚያም ዓመት መገባደጃ፣ ሜሪ እና ቤተሰቧ ወደ ኢንዲፔንደንስ፣ ምዙሪ ተዛወሩ። እርሷም የቤተክርስቲያን አባላት የትእዛዛቱ መጽሐፍ የተሰኘን አዲስ መጽሐፍ በአንድነት መጠረዝ ሲጀምሩ በማየቷ ተደሰተች። ይህ መፅሐፍ ኢየሱስ ኪርስቶስ ለነቢዩ ጆሴፍ ስሚዝ የሰጠውን ብዙ ራዕዮችን የያዘ ነው።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 6770፥1–4Saints [ቅዱሳን]1፥178

የተበሳጩ ሰዎች ማተሚያ ቤቱን ሲያፈርሱት።

ነገር ግን በኢንዲፔንደንስ የነበሩ አንዳንድ ሰዎች ቤተክርስቲያኗን አልወደዱም ነበር። እነርሱም ቅዱሳኑ ለቀው እንዲወጡ ይመኙ ነበር። አንድ ቀን፣ ብስጩ ሰዎች የትእዛዛቱ መጽሐፍ እየታተመ የነበረበትን ህንጻ ሰብረው ገቡ። የማተሚያ ማሽኑን በመስኮት ወረወሩት እና የመፅሐፍ ትእዛዛት ገጾች ጎዳና ላይ በታተኗቸው።

Saints [ቅዱሳን]1፥177–78

ሜሪ እና ካሮሊን ከአጥሩ በስተጀርባ ተደብቀው።

ሜሪ እና እህቷ ካሮሊን ከአጥሩ በስተጀርባ ሆነው እየተመለከቱ ነበር። ሜሪ ለካሮሊን፣ ገጾቹ ከመጥፋታቸው በፊት ልታገኛቸው እንደፈለገች ነገረቻት። ካሮሊን የተበሳጩትን ሰዎች ፈርታቸው ነበር። ‘’ይገድሉናል፣’’ በማለት ተናገረች። ነገር ግን ሜሪ እና ካሮሊን እነዚያ ገጾች በላያቸው ላይ የእግዚአብሔርን ቃላት እንደያዙ ያውቁ ነበር።

Saints [ቅዱሳን]1፥178

ሜሪ እና ካሮሊን እየሸሹ።

እህቶቹ ሰዎቹ ማየት እስከማይችሉበት ጊዜ ድረስ ጠበቁ። ከዚያም ወደ ጎዳናው ሮጡ እና መያዝ የሚችሉትን ያህል ገጾች ሰበሰቡ። በፍጥነት በመሮጥ ላይ እያሉ፣ የተወሰኑ ሰዎች አዩአቸው ከዚያም እንዲያቆሙ መጮህ ጀመሩ። ሜሪ እና ካሮሊን ገጾቹን አጥብቀው ይዘዋል እናም በአቅራቢያው ወዳለው የበቆሎ ማሳ በቻሉት ፍጥነት ሮጡ።

Saints [ቅዱሳን]1፥178–79

ሜሪ እና ካሮሊን በበቆሎው ማሳ ውስጥ ተደብቀው።

ሁለት ወንዶች እህቶቹን በበቆሎው ማሳ ውስጥ አሳደዷቸው። በቆሎው በጣም ረዥም ነበር፣ ሚሪ እና ካሮሊን የሚሄዱበትን ማየት አልቻሉም ነበር። ራሳቸውን ወደ መሬት ጣሉ እና ገጾቹንም በሰውነታቸው ደበቋቸው። ሁለቱ ወንዶች በበቆሎው መሃል እየተራመዱ ሲፈልጓቸው በቀስታ አዳመጡ።

Saints [ቅዱሳን]1፥179

ሜሪ እና ካሮሊን ጆሴፍ ስሚዝን ሲያዳምጡ።

ወዲያውኑም ወንዶቹ ተስፋ ቆረጡ። ሜሪ እና ካሮሊን ደህና ሆኑ። እነርሱም የጌታን ራዕይ ገጾች ለመፅሐፈ ትእዛዛት እንዲገኙ አተረፏቸው። ዛሬ እነዚያ ራዕዮች በትምህርት እና ቃል ኪዳኖች መጽሐፍ ውስጥ ናቸው።

Saints [ቅዱሳን]1፥179