‘’ኑወል እና አን ውትኒ ከነቢዩ ጆሴፍ ጋር ተገናኙ፣’’ የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች (2024 [እ.አ.አ])
‘’ኑወል እና አን ውትኒ ከነቢዩ ጆሴፍ ጋር ተገናኙ፣’’ የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች
ጥቅምት 1830–የካቲት 1831 (እ.አ.አ)
ኑወል እና አን ውትኒ ከነቢዩ ጆሴፍ ጋር ተገናኙ
በእምነት የሚሰጡ ጸሎቶች በጌታ ይመለሳሉ
አን እና ኑወል ውትኒ በከርትላንድ፣ ኦሀዮ መጋዘን ነበራቸው። አን ወደ ቤተክርስቲያን በመሄድም ሆነ ስለጌታ በመማር አላደገችም፣ ነገር ግን እርሱን ለማወቅ ፈልጋለች። እርሷ እና ኑወል ካተጋቡ በኋላ፣ ብዙ ጊዜ ጸልየዋል እና ጌታ እንዲመራቸው ጠይቀዋል።
Saints [ቅዱሳን]፣ 1፥111–12
በአንድ ሌሊት በጸሎት ላይ ሳሉ፣ አን እና ኑወል ራዕይ አዩ። በራዕዩም ውስጥ፣ በቤታቸው አናት ላይ ደመና አረፈ። የእግዚአብሔር መንፈስ ሞላቸው። ደመናውም ከበባቸው። ከዚያም ከሰማይ የሚመጣ ድምጽ ሰሙ፡፡ ‘’የጌታን ቃል ለመቀበል ተዘጋጁ፣ እየመጣ ነውና’’ በማለት ነገራቸው።
Saints [ቅዱሳን]፣ 1፥111
ከትንሽ ጊዜ በኋላ፣ ፓርሊ ፕራት ወደ ከርትላንድ መጣ። እርሱ እና የእርሱ የሚስዮን አጋሮች የኢየሱስ ክርስቶስን ወንጌል አስተማሩ። እያስተማሩ ያሉትን ልክ እንደሰማች፣ ወዲያውኑ እውነት እንደሆነ አወቀች። ዜናውን ለኑወል ለማጋራት ወደ ቤቷ ሄደች። ብዙ ሳይቆይም ተጠመቁ።
Saints [ቅዱሳን]፣ 1፥112
ከሁለት ወራት በኋላ፣ አንድ ወንድ እና አንዲት ሴት ወደ ኑወል መጋዘን መጡ። ኑወል አላወቃቸውም፣ ነገር ግን ሰውየው የኑወልን እጅ ጨበጠ እና ኑወልን በስሙ ጠራው። ሰውየውም፣ ‘’እኔ ነቢዩ ጆሴፍ ነኝ’’ አለ። ጌታ የኑወልን ጸሎቶች እየመለሰ እንደሆነ ገለጸ። እርሱ አንን እና ኑወልን እንዲያገኟቸው ኤማን እና ጆሴፍን ልኳቸዋል።
Saints [ቅዱሳን]፣ 1፥113
ኑወል እና አን ራዕያቸው እውን እየሆነ መሆኑን አወቁ። እነርሱም ጆሴፍ እና ኤማን በቤታቸው አብረው እንዲኖሩ ጠየቋቸው። አን እና ኑወል ኢየሱስን እና ወንጌሉን ወደዋል። ያላቸውን ሁሉ ለቅዱሳን እና ለጌታ ቤተክርስቲያን ሰጥተዋል።
ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 38፥23–27፣ 34–42፤ Saints [ቅዱሳን]፣ 1፥114