በቅዱሳት መጻሕፍት ውስጥ የሚገኙ ታሪኮች
ሆውንስ ሚል


“ሆውንስ ሚል፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች [2024 (እ.አ.አ)]

“ሆውንስ ሚል፣” የትምህርት እና ቃል ኪዳኖች ታሪኮች

ጥቅምት 1838–የካቲት 1839 (እ.አ.አ)

ሆውንስ ሚል

ጥቃት እና ተዓምር

ዊላርድ ስሚዝ እና ቤተሰቡ በሆውንስ ሚል

ዊላርድ ስሚዝ 11 ዓመቱ ነበር። ቤተሰቡ በሆውንስ ሚል፣ ሚዙሪ ከሌሎች ቅዱሳን ጋር ይኖር ነበር። በቅርቡም ከቅዱሳን ጋር በሩቅ ምእራብ መሰባሰብን ይፈልጉ ነበር።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 115፥7–8ቅዱሳን1፥347–48

ሰዎች በሆውንስ ሚል የነበሩ ቅዱሳንን ለማጥቃት ሲመጡ።

አንድ ቀን፣ ዊላርድ ከአባቱ እና ከወንድሙ፣ ሳርዲየስ እና አልማ ጋር ነበር። በድንገትም፣ የመሳሪያ ተኩስ እና ጩኸት ሰሙ። ሰዎች ቅዱሳንን ለማጥቃት መጥተዋል።

ቅዱሳን1፥348–49

ቅዱሳን በሆውንስ ሚል ከነበሩ አጥቂዎች ሲደበቁ።

እያንዳንዱ ሰው ከለላን ፍለጋ ሮጠ። አያሌ ወንዶች እና ህጻናት በብረት ቀጥቃጭ ሱቅ ውስጥ ተሸሸጉ። የዊላርድ አባት እና ወንድሞች ወደዚያው ገቡ፣ ነገር ግን ዊላርድ ከእነርሱ ተለየ። እርሱም በአንድ የማገዶ ክምር ጀርባ ተሸሸገ። በዙሪያው ሁሉ የመሳሪያ ተኩስ ሰማ።

ቅዱሳን1፥349353

ዊላርድ እየሮጠ

ዊላርድ ለመሸሸግ ከስፍራ ወደ ስፍራ ሮጠ። በመጨረሻም የተኩስ ድምጹ ቆመ፡፡ አጥቂዎቹ ሆውንስ ሚልን ለቀው ሄዱ።

ቅዱሳን1፥353

ዊላርድ በብረት ቀጥቃጭ ሱቅ ውስጥ።

ዊላርድ ቤተሰቡን ፍለጋ ወደ ብረት ቀጥቃጭ ሱቅ መጣ። አባቱ እና ሳርዲየስ ተገድለው ነበር። ነገር ግን የዊላርድ ትንሽ ወንድም አልማ በህይወት ነበር።

ቅዱሳን1፥353

ዊላርድ ወንድሙን አልማን ተሸክሞ።

አልማ ጭኑ ላይ ተመትቶ ነበር። ክፉኛ ተጎድቷል። ዊላርድ አልማን ተሽክሞ የቤተሰቡ ድንኳን ወዳለበት ወሰደው።

ቅዱሳን1፥353–54

አማንዳ ስሚዝ ለልጇ አልማ እየጸለየች።

የዊላርድ እናት፣ አማንዳ፣ የአልማን ጭን እንዴት መርዳት እንዳለባት አላወቀችም። ነገር ግን እግዚአብሔር እንደሚያውቅ አውቃለች። ጸለየች፣ እናም በትክክል ምን ማድረግ እንዳለባት የሚነግራትን ድምጽ ሰማች።

ቅዱሳን1፥354

አማንዳ የአልማን ቁስል ስትንከባከብ።

አማንዳ የአልማን ቁስል በአመድ አጠበች። ከዚያም አንዳንድ የዛፍ ስር ነቅላ በቁስሉ ላይ አኖረች። ጭኑን በልብስ ጠቀለለች። ‘’እንደዚህ ተጋደም፣ እንዳትንቀሳቀስ፣’’ በማለት ተናገረች፣ ‘’እና ጌታ ሌላ ጭን ያበጅልሃል።’’

ቅዱሳን1፥354–55

አማንዳ እርዳታን በመፈለግ ጸለየች።

በኋላም፣ የሀገር ገዢው ቅዱሳን ሚዙሪን ለቀው መውጣት እንዳለባቸው አለዚያም እንደሚገደሉ አወጀ። ነገር ግን የአልማ ጭን እስካሁን መሻሻል አላሳየም። አማንዳ ጸለየች እናም የጌታን እርዳታ ጠየቀች። አንድ ድምጽ ኢየሱስ ቤተሰቧን በፍጹም እንደማይተው ነገራት። አማንዳ ምንም ነገር ሊጎዳት እንደማይችል ተሰማት።

ትምህርት እና ቃል ኪዳኖች 88፥83ቅዱሳን1፥372378–79

ጭኑ ከተፈወሰ በኋላ የአልማ ሲረማመድ።

ከጸለየች በኋላ ወዲያውኑ፣ አማንዳ ልጆቿ ሲጮሁ ሰማች። እነርሱን ፍለጋ ሮጠች፣ በሮጠችም ጊዜ አልማ በስፍራው እየሮጠ ነበር። ‘’ደህና ነኝ፣ እናቴ፣ ደህና ነኝ!’’ አለ። ጭኑ ተፈውሷል! ይህም ከጌታ ዘንድ የሆነ ተዓምር ነበር። አማንዳ እና ልጆችዋ ከሌሎች ቅዱሳን ጋር የተሻለ ስፍራን በመፈለግ ሚዙሪን ለቀው ሄዱ።

ቅዱሳን1፥379